Showing posts with label Amharic. Show all posts
Showing posts with label Amharic. Show all posts

Sunday, August 12, 2018

በሻሸመኔ ከተማ በተፈጠረ መገፋፋትና መረጋገጥ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በርከት ያሉ ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሷል


በሻሸመኔ ከተማ በተፈጠረ መገፋፋትና መረጋገጥ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በርከት ያሉ ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሷል
አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 6፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ ከተማ በተፈጠረ መገፋፋትና መረጋገጥ የሰዎች ህይወት እና አካል ላይ ጉዳት መድረሱ ተገለፀ።
አደጋው የደረሰው የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ዳይሬክተር አቶ ጃዋር ሞሃመድ እና ሌሎች የቡድኑ አባላት አቀባበል ለማድረግ በከተማዋ በተዘጋጀ ስነ ስርዓት ለይ መሆኑን የኦህዴድ የገጠር ፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ አዲሱ አረጋ አስታውቀዋል።
በአደጋውም የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በርካቶች ላይ ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት መድረሱንም አቶ አዲሱ ገልፀዋል።
በአቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ በተፈጠረ መገፋፋትና መረጋገጥ በደረሰው አደጋ ህይወታቸው ላለፈ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎችም የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል።
ከአደጋው ጋር ተያይዞም አንድ የሻሸመኔ ከተማ የፀጥታና አስተዳደር በሮ ተሽከርካሪ በእሳት መጋየቱንም አቶ አዲሱ አስታውቀዋል።
ተሽከርካሪው ፀጥታ የማስከበበር ስራ ላይ በተሰማራበት ወቅት ቦምብ ጭኗል በሚል በተሳሳተ መረጃ በእሳት መጋየቱን አቶ አዲሱ ገልፀዋል።
ሆኖም ግን በተሽከርካሪው ላይ ምንም አይነት ቦምብ እንዳልነበረ ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ማረጋገጣቸውንም አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅትም አደጋው ጋር ተያይዞ ወጣቱን በመምሰል የህገ ወጥነት እንዲስፋፋ መንገድ የመዝጋት፣ የዝርፊያ እና በፍቅር አብሮ የኖሩ ብሄር ብሄረሰቦች ላይ ጉዳት ለማድረስ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ምልክቶች መታየታቸውንም ገልፀዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች እና ወጣቶች ከዚህ ተግባር በመቆጠብ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።

Friday, August 3, 2018

ተስፋ ሰጭው የሳይንስ ትግበራ -የሮኬት ሙከራ

ተስፋ ሰጭው የሳይንስ ትግበራ፡፡

‹‹የማዕከሉ ሙከራዎች ኢትዮጵያ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ ለመድረስ ላሰበችው እቅድ አቅም ይሆናል።››
‹‹የተማሪዎችን ፈጠራ በእውቀት እና በገንዘብ የምንደግፍበት ወቅት ነው›› የባሕርዳር ሳይንስ ማበልፀግያ ማዕከል፡፡

ሳይንስ ለችግሮች መፍትሄ ለማምጣት የምንጥርበት የእውቀት እና ክህሎት መድረሻ ነው። የሁሉም ስኬታማ ሳይንስ መነሻው ችግር ፣ ትንንሽ ሙከራዎች እና የሚያድጉ ፍላጎቶች ናቸው።
በባሕርዳር ሳይንስ ማበልፀግያ ማዕከል ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች ሮኪቶችን ማምጠቅ የሚቻልበትን ሳይንሳዊ ትግበራ እየሰሩ ነው።
የ11ኛ ክፍል ተማሪዎቹ ናሆም ፈረጃ እና ኑር አህመድ አባይ በውሃ ሃይል እምቅታ እና በኬሜካል የሚመጥቁ ሮኪቶችን ሰርተዋል።
የተማሪዎቹ ግኝት ከሶስት ዓመታት በላይ የወሰደ ሳይንሳዊ ግኝት ነው የሚሉት የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋየ ሽፈራው ሳይንስን መተግበር እንደተጀመረ ማሳያ ነው ይላሉ።
ዶክተር ተስፋየ እውነታው ግን ተማሪዎቹ በውሃ እምቅታና በኬሜካል ሊያመጥቁ የሚችሉ ትግበራዎችን በግሃድ ማሳየት የሚችሉበት አቅም ፈጥረዋል።
የሚሰሩት ቁሳቁስ በአከባቢው ከሚገኙት በመሆኑ የሚወነጨፈው ሮኪት ለሃገራዊ ጥቅም የሚውል አይደለም። እንደነዚህ አይነት ሙከራዎችን ግን ከትንሽ እስከ ትልቅ ችግር ለመፍታት እንዲያስችል ወደ ምርት ለማስገባት እገዛዎች ያስፈልጉናል ብለዋል።
የተማሪዎችን ፈጠራ ጥቅም ላይ ለማዋል ተጨማሪ እውቀት ማበልፀግ እና በገንዘብ የምንደግፍበት ወቅት ላይ ደርሰናል። ኢትዮጵያ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ ለመድረስ ላሰበችው እቅድም አቅም የሚያጎለብቱ በመሆኑ ተማሪዎቹ የተሻለ ስልጠና እንዲያገኙ በገንዘብ እንዲደገፉ መስራት እንደሚያስፈልግ ዶክተር ተስፋየ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡-ግርማ ተጫነ






Sunday, July 29, 2018

የአቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ



የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።

የታላቁ ኅዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ። አዲስ አበባ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል በተካሔደው የቀብር ሥነ-ሥርዓት የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ፣ ምክትል ጠቅላይ ምኒስትር ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ሹማምንት ተገኝተዋል።  
ድንገተኛ ዜና ዕረፍታቸው ከተሰማ ጀምሮ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የተፈጠረው ሐዘን እና  ቁጭት አለመብረዱ በመስቀል አደባባይ በተካሔደው የሽኝት መርኃ-ግብር ላይ ታይቷል። በሽኝት መርኃ-ግብሩ ላይ ገዳዮቻቸው ለፍርድ ይቅረቡ የሚሉ በርካታ ድምፆች መሰማታቸውን የአይን ዕማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። አቶ ስመኘው ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም መስቀል አደባባይ አካባቢ በተሽከርካሪያቸው ውስጥ ሞተው መገኘታቸው ከተሰማ በኋላ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ሐዘን ተፈጥሯል። ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ የምኅንድስና ባለሙያው አቶ ስመኘው በቀለ የሞት "ዜና ልብ ይሰብራል" ሲሉ ተናግረዋል።
የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።
የ53 አመቱ አቶ ስመኘው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሲቪል ምኅንድስና ያገኙ ሲሆን በግልገል ጊቤ 1 እና ግልገል ጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች መርተዋል። ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ በተባለው ቦታ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የታላቁ ኅዳሴ ግድብ እስከ ዕለተ-ሞታቸው በኃላፊነት ሲመሩ ቆይተዋል።
ከአባታቸው አቶ በቀለ አይናለም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘነቡ አብተው መስከረም 3 ቀን 1957 ዓ.ም. በቀድሞው ጎንደር ልፍለ ሀገር ጠዳ ወረዳ ልዩ ስሙ ማክሰኚት ከተባለ ተወለዱ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በእንፍራንዝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደሴ ቅዳሜ ገበያ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወልዲያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መከታተላቸውን በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተነበበው የሕይወት ታሪካቸው ይጠቁማል።

Monday, May 21, 2018

በኢትዮጵያ ግብረ ሰዶምን ለማስፋፋት ፕሮቴስታንት አዋጇን በይፋ ጀምራለች

በኢትዮጵያ ግብረ ሰዶምን ለማስፋፋት ፕሮቴስታንት አዋጇን በይፋ ጀምራለች


Michal Fattal
Image result

"ሰው መንፈስ ነው" የሚለው የፕሮቴስታንቱ ትምህርት የሰዶማውያን አስተምህሮ ነው። በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሥር እየሰደደ የመጣውና ብዙ ክርስቲያኖችን እያወዛገበ ያለው የእምነት ቃል እንቅስቃሴ/ Word faith movement / አስተምህሮ በአሁን ሰዓት በፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ውስጥ ከፍተኛ ስፍራ ተሰጥቶት ታላላቅ በሚባሉ ፓስተሮች ሳይቀር ይህ እንግዳ የሆነ አጋንንታዊ ትምህርት በየመድረኮቻቸው በስፋት እየተሰበከ ነው።የእምነት ቃል እንቅስቃሴ በርካታ ክህደትና ኑፋቄ ያለው አስተምህሮ ሲሆን በዋነኛነት "ሰው መንፈስ ነው ነፍስ አለው በሥጋ ውስጥ ያድራል"የሚለው ትምህርት ግን ግብረ ሰዶማውያን የፈጠሩትና ሰዶማዊነትን በሃይማኖት ሽፋን ለማስፋፋት ሆን ተብሎ የታቀደ አጋንንታዊ አስተምህሮ ነው። ሰው መንፈስ ነው በሥጋ ውስጥ ያድራል የሚሉት የፕሮቴስታንት ሰባኪዎች በሥጋችን የምንሰራው ማናቸውም ዓይነት ኃጢአት እና ነውር ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ኅብረት አያቋርጠውም፤ እኛም የእግዚአብሔር ልጆች በመሆናችን ላይ የሚያመጣብን አንዳችም ዓይነት ተጽኅኖ የለውም የሚልና ትውልዱን መረን የለሽ የሚያደርግ በድፍረት ኃጢአት ክርስቲያኖች እንዲመላለሱ የሚያበረታታ በማር የተለወሰ መርዝ ነው። ሰው መንፈስ ነው በሥጋ ውስጥ ያድራል ማለት ልክ እንደ ዳዊትና ማኅደር ወይም እንደ መጽሐፍና ቦርሳ ማለት ነው መጽሐፍ ቦርሳ ውስጥ ይቀመጣል ቦርሳው ቢቆሽሽና ቢጨቀይም መጽሐፋ ላይ የሚያመጣው ተጽኅኖ የለም የሚለው የፕሮቴስታንቱ ፍልስፍና በሥጋችን ምንም ነገር ብንፈጽም ሰው የሚባለው ዋነኛው መንፈሳችንን አያረክሰውም አያቆሽሸውም ባዮች ናቸው። ወገኖቼ መጽሐፍ ቅዱስ "ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች ፍጻሜዋ ግን ሞት ነው" ብሎ እንደ ሚነግረን ይህ ትክክለኛ የሚመስለውና የሰዎችን ልቡና በቀላሉ ለማሳመን በሰይጣናዊ ጥበብ የተወጠነው ትምህርት ክርስቲያኖችን ሙሉ ለሙሉ ከእግዚአብሔር የሚለይና ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሚያራቁት የድፍረት ኃጢአትን የሚያለማምድ ክህደት ነው። ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል የሚነግረን ሥጋችንም መንፈሳችንም ለእግዚአብሔር የተቀደሰ እንዲሆን ነው እንጂ በመንፈስ ስለ መቀደስ ብቻ አያስተምረንም ። " እንግዲህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ የዚህ ተስፋ ቃል ካለን፥ በእግዚአብሔር ፍርሃት ቅድስናን ፍጹም እያደረግን ሥጋንና መንፈስን ከሚያረክስ ሁሉ ራሳችንን እናንጻ።" (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7:1)::

ሰዶማውያን በአሁን ሰዓት በየሀገሩ እየተስፋፋ የመጡትና በፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ውስጥ ሕጋዊ ጋብቻ እስከ መፈጸም የደረሱት በዚህ አጋንንታዊ አስተምህሮ ላይ በመመስረት ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ግብረ ሰዶምን ለማስፋፋት "ሰው መንፈስ ነው በሥጋ ውስጥ ያድራል"የሚለውን አስተምህሮ እያወጁና እየሰበኩ ያሉ ፓስተሮች የዲያብሎስ መንገድ ጠራጊዎች ናቸውና በጣም ልንጠነቀቃቸው ይገባል። ቅዱስ ቃሉ እንዲህ ይላል " የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።" (1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5:23) የተከበራችሁ ወገኖቼ በተለያዩ ሀገራት ፕሮቴስታንት ግብረ ሰዶምን በአዋጅ ማጽደቋን በይፋ እያየን ነው ቀጥሎ ያለው ጽሑፍ የእነርሱ የአቋም ነው።

መግለጫ

Evangelical Lutheran Church in America

The Evangelical Lutheran Church in America defines marriage as “a lifelong covenant of faithfulness between a man and a woman.” However, at its 2009 church-wide assembly, it voted to allow congregations that choose to do so to recognize and bless same-sex unions. At the same assembly, the church also adopted a social statement on human sexuality that supports a wide variety of families, including those headed by same-gender couples.

ሰዶማውያን ኢትዮጵያ ውስጥ ያላቸው ዕቅድ ምንድን ነው ? 

በ1908 አከባቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስትያንን የወንጌል ስርጨት ለመደገፍ በሚሉ የዴንሽ/የዴንማርክ/ ሚሽነሪዎች ምንፍቅናን ወደ ሀገራችን ያስገቡት የዴንማርክ ፕሮቴስታንቶች ዛሬ ከ100 ዓመት የእምነት ኢንቨስትመንት ልፋት በኋላ ዛሬም እንዳሰቡት ሳይሆን እንደተገኘ የሚያምኑት ሀቅ ነው ፤ከኢትዮጽያ ሚሽነሪዎች በኋላ ወደ ኬንያ የገቡት አካላት መሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የኬንያውያንን ዕሴት ፣እምነት እና ባህል ከኢንግሊዛውያን ጋር በመተባበር በርዘው ህዝቡን ሞራል እና ስብዕና አጥ አድርገውታል። እንግዲህ ዛሬ ላይ ላለው የኢትዮጵያ ፕሮቴስታንት ወይም ወንጌላውያን አማኞች ህብረት ትልቅ የአስተምህሮ እና የአርዓያ ምልክት የሚደረጉት የዴንማርክ ሚሽነሪዎች ናቸው ። ዛሬም ይህቺ ሀገር ማለትም ዴንማርክ ለህብረቱ እና ለአንዳንድ የፕሮቴስታንት ዓብያተክርስትያናት የትምህርት የሎጀስቲክ እና የፋይናንስ ድጋፍ ከሚያደርጉ ሀገራት መካከል ቀዳሚዋ ናት ።


የዴንማርክ የዕምነት እና የግብረ ሰዶማዊነት ፕሮፋይል

ዴንማርክ ምንም እንኳን ላይ ላዩን ቅዱስ የምትመስል ሀገር ብትሆንም ውስጧ ግን እጅግ በጣም በክፋት እና በኃጢአት የደረጀ ነው ። ከሀገሪቷ 5.7 ሚልዬን ህዝብ መካከል በዋናነት ፕሮቴስታንት 75.2% ማለትም 4,275,000፣ በትንሳኤ ሙታን የማያምኑ agnostic 9.1% ማለትም 518,700፣ በእግዚአብሄር የማያምኑ Atheist 10.6 % ማለትም 604,000 ናቸው። ዴንማርክ የፕሮቴስታንት የበላይነት ስላለ የዴንማርክ ሕገ መንግስት እና የሀገሪቱ መንግስት የፕሮቴስታንት ተልዕኮን፣ ወንጌልን እና ስርዓትን የመደገፍ ብሄራዊ ግዴታ አለበት ። በእዚህ መሰረት ዴንማርካውያን እና የዴንማርክ መንግስት በሥሩ በአፍሪካ ብቻ 259 የዓብያተክርስቲያናትን ህብረት እና ቤተክርስትያን ይደግፋል፣ ስኮላር ሺፕ ይሰጣል፣ ከእዛም ከፍ ሲል የመኖርያ ፍቃድ ይሸልማል

ዴንማርክ እና ግብረሶዳማውያን

ዴንማርክ ከዓለም ሀገራት መካከል ግብረሶዶማዊነትን በማስፋፋት እና እውቅና በመስጠት እጅግ በጣም ቀዳሚዋ ናት ። ይህም የሚያሳዩው ከ1925 ዓ.ም ጀምሮ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ህጋዊ አድርጋለች፣ 1981 ጀምሮ የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን ፈቅዳለች፣ 2005 ጀምሮ ግብረሰዶማውያን በጉድፈቻ ልጅ የማሳደግ መብት ተሰጥቷቸዋል፣ በ2006 ዓ.ም ግብረሰዶማውያን ፆታቸውን በሰርጀሪ የመቀየር መብት ተሰጥቷቸዋል፣ ከእዚህ በተቃራኒው ግብረሶዶማውያንን ማግለል፣ ልክ እንደእኛው ሀገር ሰዶማውያን በሚሰደቡበት ቃል መስደብ፣ ልዩ በሆነ እንቅስቃሴ እና አትኩሮት መመልከት፣ አገልግሎትን ( ለምሳሌ የአልጋ የመጠጥ የምግብ ፣ወዘተ) መከልከል ዘብጥያ የሚያስወርድ ወንጀል ነው።

ዴንማርክ በኢትዮጵያ

እንግዲህ ዴንማርክ እና ዴንማርካውያን ከኢትዮጵያውን ጋር የተዋወቁት በክርስትናዊ ምንፍቅና ነው ።ከእዛ ጊዜ ጀምሮ በመንፈሳዊ ጠላትነታቸው አንዱ ስኮናውን ሊመታ ሌላኛው አፈር ሊልልስ ተማምለው ርስት ላለማስነጠቅ ውጊያ ላይ ከሆኑ ሰነባብተዋል ። በፕሮቴስታንት ቤተእምነት በኩል የሸረበችው ህዝቡን ከሞራል እና ከግብረግብነት ሜዳ ለማውጣት የወጠነችው ውጥን ፍሬ እንደማያፈራ የገመተችው ዴንማርክ ዛሬ በተቀደሰችው ሀገራችን መዲና በሆነችው አዲስ አበበ ላይ የግብረሰዶማውያንን ባንዲሪ ከሀገሯ ሰንደቃላማ ከፍ አድርጋ በማውለብለብ በኤንባሲዋ በኩል ፍላጓቷን ገልፃለች ።

ኢትዮጵያውያን ሆይ ግብረሰዶማዊነት አጸያፊ ነውርና ወንጀል በሆነበት ሀገራችን ይህቺ ፕሮቴስታንታዊ መንግስት የሆነችው ዴንማርክ በሀገሪቷ ላይ የሰማይ መስኮት ልታስከፍት እና የዲን እሳት ልታዘንብ ዛሬ ግብረሰዶማዊነትን በምድራችን ላይ አውጃለች እያልኩሁ ነው ። መፃፍ ቅዱስ በቃሉ"" ከሴሰኞች ጋር እንዳትተባበሩ በመልእክቴ ጻፍሁላችሁ።1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5 : 9"" እንዳለው በእምነት እና በእውነት ክርስቶስን የምትሹ ፕሮቴስታንታውያን እጃችሁን እና ወንጌላችሁን ከእነዚህ ወገኖች አርቁ ።ከሴሰኞች እና ከፀረ-ክርስቲያናዊ ቡድን ጋር ብትተባበሩ ግን ከክፋታችሁ በላይ እየከፋችሁ እንዳትሄዱ ተጠንቀቁ። ምክንያቱም ቃሉ ""ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች፥ እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ።2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3 : 13"" ይላል።

እንግዲህ ወዳጄ ሁላችንም ሀገራችንን እና እምነታችንን የመጠበቅ ግዴታ አለብን ።ይህም በፀሎት፣ ነቅቶ በመጠበቅ እና ሀሰተኛን በመለየት እንዲሁም ከሰው አስተሳሰብ ከሆነ ፍልስፍናዎች ወጥተን የክርስቶስ የፍቅሩን ትዕዛዛት በመጠበቅ ሀገራችንን በቅድስና ልናቆም ይገባል ። ቃሉም "" እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ።" ይላል።የዮሐንስ ወንጌል 15 : 10

የተከበራችሁ ፕሮቴስታንት ወገኖቼ አብዛኛው ፓስተሮች ሃይማኖተኛ አትሁኑ የእምነት ሰዎች ብቻ ሁኑ ሃይማኖተኛነት የተቋም አጥር ነው የሚሉት ትውልዱን ከ ውጭ በመጣ እርኩሰት ውስጥ ለማስገባት ነው።ፓስተሮቹ ሃይማኖተኛነት አይድንም የሚለውን ስብከት ኮፒ አድርገው የሚሰብኩት ከነጮች ነው።ስለዚህ እስከዛሬ ድረስ የተታለላችሁት ይበቃል ወደ እናት ኦርቶዶክሳዊ ተዋህዶ ሃይማኖት ተመልሳችሁ በቅድስና ከእግዚአብሔር ጋር ቀሪ ዘመናችሁ ኑሩ።የመዳን ቀን ዛሬ ነው ልባችሁን መልሱ በፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ሰዶማዊነት፣ጥንቆላ፣ዝሙት እጅግ እየተስፋፋ መጥቷል ወደ ፊት ትውልዱን እግዚአብሔር የለም የሚል ክህደት ውስጥ የሚከቱት እነዚሁ የፕሮቴስታንት ነውረኛ አገልጋዮች ስለሆኑ እግዚአብሔር ይህችን ዕለት ለነስሐ ሰጥቷችኋልና በፍጥነት ተመለሱ።አውሮፓውያንን እምነት የለሽ ያደረጋቸው ከፕሮቴስታንት ቤተ እምነት የተነሳው የሐሰተኛ ነቢያት ውሸት፣የአጭበርባሪ ፓስተሮች ሌብነት እና በቤተ እምነቱ ውስጥ በየጊዜው የሚነሳው እንግዳ ትምህርት ነው። ወገኔ ሆይ ንቃ!!!

እባካችሁ ይህንን ጽሑፍ ሼር በማድረግ ትውልዱን ከእሳት ነጥቀን እናድን

Tuesday, May 15, 2018

ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አቅርበው ስልጣን ላይ ያሉ ሹመኞች ጉዳይ እየተጣራ ነው

ዋዜማ ራዲዮ -በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ከፍተኛ የመንግስት ስልጣን ይዘው የሚገኙ ግለሰቦችንና ሌሎች የክልልና የፌደራል መንግስት ሰራተኞችን የትምህርት ማስረጃዎች የማጣራት ስራ ተጀመረ።
ብሄራዊ የመረጃና ደህንነት ኤጀንሲ (INSA) ከትምህርት ሚንስቴር ጋር እያደረገ ባለው ምርመራ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሀሰተኛ ሰነድ በማቅረብ ተለይተዋል።
Tilaye Gete (PhD) – Photo: MoE
ከቅርብ ወራት ወዲህ በኢትዮጵያ ክልሎችን ጨምሮ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ለበርካታ ዓመታት በተጭበረበረና በሐሰት የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው በሚሰሩ ሰራተኞችና አመራሮች ላይ የተጀመረው የማጽዳት ዘመቻ ወደ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከፍ ብሎ መታየቱ አንዳንድ ባለስልጣናትን እያሰቆጣ መሆኑን ዋዜማ ከምንጮች ለማወቅ ችላለች፡፡
ዘመቻው በርካታ ስመ-ጥር ባለስልጣናትን ተጠያቂ ማድረጉ ስለማይቀር ምርመራው እንዲቆም ወይም እስካሁን በተደረገው ማጣራት ላይም ከህግ ይልቅ በፖለቲካዊ ውሳኔዎች ታይቶ እንዲታለፍ አንዳንድ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ጫና እያሳደሩም ይገኛሉ፡፡
በፌደራል መንግስት ስር ያሉ ተቋማት ውስጥ በከፍተኛና በመካከለኛ የአመራር ደረጃዎች ያሉ ኃላፊዎች በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተሹመው በመገልገል ላይ ካሉት የበርካታ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለኢህአዴግ ጽ/ቤትና ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ተልኳል ተብሏል፡፡
በዚሁ የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ባለቤት ናቸው ተብለው የተለዩት ለዓመታት ከመምሪያ ኃላፊነት እስከ ሚኒስትር ዲኤታነት እስከ ሚኒስትርነት ባሉ ማዕረጎች በኃላፊነት ተሹመው በማገለገል ላይ ያሉ መሆናቸውም ታውቋል፡፡
ከዚሁ አነጋጋሪው የሰነድ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ የትምህርት ሚኒስቴር ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመለየት የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት ከመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ጥላዬ ጌጤ ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ጥላዬ በፓርላማ ቀርበው ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተጠቅመው ወደ መንግስት ቢሮ የገቡ የስራ ሀላፊዎችንና ሰራተኞችን ለመቆጣጠርና ማስረጃዎቹንም ለመለየት የተጀረመው ስራ አልቆ በዚህ አመት ስራ ይጀምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡ ስራው ከጠናቀቀ በኋላ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዘው በስራ ላይ የተገኙትን በህግ ተጠያቂ ማድረግ እንደሚጀመርም ተነግሯል፡፡
በኦሮምያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ በሁለት ዙር ሲያጣራ ቆይቷል፡፡ በተደረገው የማጣራት ስራም በክልሉ ከ6,400 በላይ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዘው የተቀጠሩ ሰራተኞች ራሳቸውን አጋልጠው ይቅርታ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡
ሌሎች 8,300 የመንግስት ሰራተኞች ደግሞ የትምህርት ማስረጃቸው ሀሰተኛ እንደሆነ ተጠቁሞባቸው እየተጣራ መሆኑም ተሰምቷል።
በጋምቤላ ክልልም ባለፈው አመት በተደረገ ማጣራት የክልሉ የትምህርት ቢሮ ሀላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ባለስልጣናትና ሰራተኞች በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተሹመውና ተቀጥረው እንደሚሰሩ ተደርሶባቸዋል፡፡
አሁን የትምህርት ሚኒስትር ከመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ጋር ጀመርኩት ያለው የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመቆጣጠር የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት ሲጠናቀቅ በሁሉም የትምህርት ማሰልጠኛ ተቋማት ስራ ላይ ይውላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ዛሬ ለመንግስት ባለስልጣናት ማሳሰቢና ገለጻ ሰጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ዛሬ ለመንግስት ባለስልጣናት ማሳሰቢና ገለጻ ሰጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ዛሬ ረፋዱን(ግንቦት 7) በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ለተሰበሰቡ የተለያዩ
የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በስራዎቻቸውና አሰራር ዙሪያ ገለጻና ማሳሰቢያ ሰጡ ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ መድረክ ላይ የራሳቸውን ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፤ በዚሁ ጽሁፋቸውም የአመራር ጥበብን በተመለከተ ገለጻ አድረገዋል። የህዝበ አገልጋይ ምን አይነት ሰብዕና ሊላበስ እንደሚገባና ምነ አይነት አገልግሎት በምን አይነት ጊዜና ቦታ መስጠት እንዳለበትም በተለያዩ አብነቶች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ገለጻቸው ወቅት እንዳሉትም፤ ሳምንታዊው የካቢኔ ስብሰባ ከአርብ ወደ ቅዳሜ መለወጡንና ሚኒስትሮች አርብ በስብሰባ ስም ጊዜ ማባካን እንደሌለባቸውና መደበኛ ስራቸውን እንዲሰሩ አሳስበዋል። አገሪቷ እያደገች መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ አድጋለች ከማለት ባሻገር በተጨባጭ ህዝቡ ምን ያህል ተጠቅሟል የሚለውን መፈተሽና ማረጋገጥ አለብን ሲሉም አስታውቀዋል። እያንዳንዱ የመንግስት አመራርም አሰራሩን ግልጽና ለህዝብ የማይደበቅ ማድረግ እንደሚገባውም ዶክተር አብይ አሳስበዋል። እያንዳንዱ ሚኒስትር ከዚህ በኋላ ለስብሰባ ሲመጣ በቂ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባው የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ሚኒስትር ሃሳብ አመንጪ እንጂ አቃቂር አውጭ አይደለም” ሲሉም ነው አጽንኦት የሰጡት። ከባለስልጣናት ጉዞ ጋር በተያያዘም ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተለይም በውጭ አገራት ባንኮች አካውንት ያላቸው ባለስልጣናት በአካውንቶቻቸው ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑንና ለዚህም አገራት ትብብር እያደረጉ መሆናቸውን
አስታውቀዋል። ከዚህ በኋላም የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ልዩ ልዩ ቋሚ ኮሚቴዎች ከሚከታተሏቸው ሚኒስቴር መስሪያቤቶች ጋር የስራ
ስምምነት መፈጸም እንደሚገባቸውና ስራቸውን በዚህ አግባብ እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስተሩ ከስብሰባው በሁዋላ ባለስልጣናቱን ከአዳራሽ ይዘው በመውጣት በአጼ ሚኒሊክ፣ በአጼ ኃይለሥላሴ እና
በደርግ ዘመን የተለያዩ ታሪካዊ ድርጊቶች የተፈጸሙባቸው በቤተመንግስት የሚገኙና እስካሁን ድረስ ዝግ የነበሩ የተለያዩ
ክፍሎችን አስከፍተው እንዲጎበኟቸው አድርገዋል።
በዚህም ባለስልጣናቱ የነገስታቱን የግብር ቤቶች፣ አጼ ሀይለስላሴ የተገደሉበትን፣ የደርግ ጄኔራሎች የተረሸኑባቸውን
ክፍሎች በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት ጎብኝተዋል።

ምንጭ ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት



Monday, May 14, 2018

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከእስር ለመፍታት ተወስነ

በእስርና እንግልት ላይ የነበረውን የአርበኞች ግንቦት ስባት ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ከእስር ለመፍታት ተወስኖ በጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የተመራ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አመለከቱ።
መረጃውን ለዋዜማ ያደረሱና ከጉዳዩ ጋር ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደነገሩን አቶ አንዳርጋቸው እንዲፈታ ውሳኔ ከተላለፈ በርካታ ቀናት ተቆጥረዋል። በቅርቡ ከእስር ይፈታል ተብሎ ይጠበቃል።
አንድ የፍትሕ ሚንስቴር ባልደረባ ካለፈው ሐሙስ ጀምሮ ጉዳዩ በመስሪያ ቤታቸው አካባቢ መነጋገሪያ እንደነበርና ጉዳዩ በከፍተኛ ባለሥልጣናት በኩል በምስጢር ተይዞ ቆይቷል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። አቶ አንዳርጋቸው ሲፈታ በቀጣይ በሚኖራቸው የፖለቲካ ሚና ላይ ንግግር መደረግ አለበት ብለው የሚያምኑ ወገኖች እንዳሉ የነገሩን እኚሁ ግለሰብ በማረሚያ ቤቶች፣ በደኅንነት መሥሪያ ቤቱ፣ ግንባሩ ውስጥ ባሉ የተለያዩ ብድኖች እና በጠቅላይ ሚንስትሩ ጽሕፈት ቤት መካከል መግባባት ለመፍጠር እየተሞከረ መሆኑን መስማታቸውን ነግረውናል። በአንዳርጋቸው ጉዳይ በአራቱ የኢህአዴግ ድርጅቶች መካከል ስለነበረ ውይይት ብዙ የተሰማ ነገር የለም። ይሁንና ብአዴን የሚደርስበትን የሕዝብ ጫና ለማስታገስ የአንዳርጋቸውን መለቀቅ ሳይገፋፋ እንዳልቀረ ይገመታል።
ስለጉዳዩ ከአንዳርጋቸው ቤተሰቦችም ሆነ ከአርበኞች ግንቦት 7 እስካሁን የተባለ ነገር የለም። ወሬው ባለፉት 3 ቀናት በስፋት መሰማት የጀመረው ውሳኔውን በተለያየ ደረጃ ያሉ ሰዎች እንዲያውቁት በመደረጉ ሊሆን እንደሚችል የዋዜማ ምንጮች ተናግረዋል። የአቶ አንዳርጋቸው መፈታት በድርጅታቸው፣ አልፎም በአገሪቱ ፖለቲካ አቅጣጫ ላይ ሊያስከትል የሚችለው ተጽእኖ ብዙዎች በቅርበት የሚከታተሉት ጉዳይ ይሆናል።
አቶ አንዳርጋቸው ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ከሰንአ አውሮፕላን ጣቢያ በየመን እና በኢትዮጵያ መንግሥት የጸጥታ ሰራተኞች ታፍኖ መወሰዱ ይታወሳል። በእስር ላይም የተለያዩ ግፍና ማሰቃየት እንደተፈጸመበት ቤተሰቦቹ እና የትግል ጓዶቹ ይናገራሉ። በተቃራኒው፣ የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር) በአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ላይ ቀርበው አንዳርጋቸው በጥሩ ሁኔታ መያዙን እንዲያውም “ከተማ ይጎበኛል፣ ላብቶፕ ተሰጥቶች መጽሐፍ እየጻፈ ነው” ብለው መናገራቸው ይታወሳል። ተመድ፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ የእንግሊዝ መንግሥት እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች አንዳርጋቸው እንዲፈታ ሲጎተጉቱ መቆየታቸው ይታወቃል።

ዋዜማ ራዲዎ

Sunday, May 13, 2018

የሺህ ማይል መንገድ በአንድ ይጀመራል

የሺህ ማይል መንገድ በአንድ ይጀመራል

የኢትዮጵያ ህዝብ የመብት ጥያቄ ወደ ህልውና ጉዳይ ተለውጦ፥ የነጻነት፣ የፍትህና የዴሞክራሲ ትግል በርትቶ፥ በኦሮሞ ፕሮቴስት የጀመረው ህዝባዊ ተቃውሞ፥ ጎንደር ላይ በፈነዳው ህዝባዊ አመጽ ወደ አማራ ተጋድሎ ከፍ በማለቱ፥ በወያኔ ኢሕአዴግ ስርዓትና በገዥዎች ላይ ከፍተኛ ስጋት ፈጠረ፥
ይህ አስደንጋጭ ክስተት መረን የለቀቀውን የሕወሃት/ኢሕአዴግ ፋሺስታዊ መንግስት የግዛት መሰረቱን ያናጋ፣ የገዥዎችን ህልውና አደጋ ላይ የጣለ በመሆኑ፥ የስርአቱ ቁንጮዎች ሳይወዱ በግድ ፈጣን የማደናገሪያ ምላሽ ለመስጠት ተገደዱ፥ በተሃድሶ ስም የተነሳባቸውን የለውጥ ትኩሳት ለማስታገስ ብዙ ድንጋይ ፈነቀሉ።
ይህ ነበር እንግዲህ በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የለውጥ ንፋስ ያመጣው፥
አንድ አጋጣሚ በመጠበቅ አንገቱን አቀርቅሮ ያደፈጠው የኦሮሞ ወጣት ቄሮ ጣና ኬኛ ኦሮሞ የኛ በሚል የአንድነት ማዕበል እየቀዘፈ ከመሃል ሸዋ እስከ ወለጋ ተጠራርቶ ጣናን ዘይሮ በውቧ ባህርዳር የአማራ ዋና ከተማ ተዝናንቶ ቁሰለኛውን ጎንደር በፍቅር እስትንፋስ ጠግኖ፥ ወጣትነት መልካም ነው ያለምንም አደራዳሪ ከአንተ በፊት እኔን ያርገኝ በሚል ቃል ዲዳን ታሪካቸውን አድሰው ተመለሱ።
የጣንን ጉብኝት ተከትሎ፥ ወጣቱ የኦሮሞ ፖለቲከኛ፥ ክልሉን ቄሮ በሚል ምትሃታዊ ስም አደራጅቶ፥ ቲም ለማን አስመርቶ፥ አብይን በቀኝ አዲሱን በእግራ አሰልፎ አቶ ለማ መገርሳ ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው በሚል አማላይ ቃል ታጅቦ እንደ ሀምሌ ዝናብ ሳያጉረመርም በገዱ ግዛት በአማራ አደባባዮች ላይ ድንገት ተከሰተ። ወያኔዎች ሱሪያቸው መላላት ጀመረ፥ የአማራ እና የኦሮሞ ትብብር ሽብር ለቀቀባቸው።
በቲም ለማ መገርሳ Team Lema Megersa እና በገዱ አንዳርጋቸው ቡድን መደጋገፍ የወያኔ ፋሽስታዊ አገዛዝ ቁንጮዎች ዓይናቸው ደም ለበሰ፥ ህዝብ አምርሯልና የፈየደው ነገር የለም እንጂ በሚስጥርም ሆነ በይፋም ሹም ሽር ለማድረግ ሞከሩ።
ከዚህ በፊት ሲጠሩት የያዘውን ሁሉ ይጥል የነበረው ገዱ አንዳርጋቸው Gedu Andargachew ያልተገመተ ጽናት አሳየ፥ በእስራት ማስፈራሪያም ሆነ በስራ ቅያሬ ከቦታው ንቅንቅ የማይል ጀግና ወጣው፥ የሰጡትን የአምባሳደርነት ሹመት ስራየን አልጨረስኩም አልቀበልም አላቸው።
ብዙም ሳይቆይ ለግዛቷ የመበታተን፣ ለህዝቧ የመጠፋፋት አደጋ ለገጠማት አገራችን ኢትዮጵያ ይታደጋል ያሉትን የፖለቲካ ሃኪም ዶክተር አብይ አህመድን ከኋላ ሸሽገው፥ አንደበተ ርቱዕ ጀግና የሆነውን የኦሮምያ ክልል አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ለማ መገርሳን አስመርቶ፥ የአማራው ክልል አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው Gedu Andargachew ለውጡን በፊታውራሪነት እየመራው መሆኑ ግልጽ ሆነ።
የሃይል ሚዛኑን ላለማስነጠቅ ወያኔ ተፍጨረጨረች ግን አልሆነም፥ ቄሮ መሃል አዲስ አበባ መግባቱን አራት ኪሎ ቤተመንግስት ወረድ ብሎ በመሌኒየም አዳራሽ በወጣቱ የኦሮሞ አቀንቃኝ ዜማ አይናቸው እስኪፈጥ ድረስ ትለቃለህ ትሰዳለህ በሚል ፉከራ ለወያኔ ማስጠንቀቂያ ሰጠ፥
ቲም ለማ እና ቲም ገዱ አዲስ አበባ ተጠርተው በኢቲቪ ማብራሪያ እንዲሰጡ፥ ጥርስ የሌለው ውሻ ሆኖ ቀረ እንጂ ለማስፈራራት ተሞከረ፥ አቶ አዲሱ Addisu Arega Kitessa የኦሮምያ ሙሁራን ይዞ፥ አቶ ንጉሱ ጥላሁን Nigussu tilahun የአማራ ሙሁራን ጋር ተደጋግፈው የወያኔውን አፈቀላጤ አፉን አስያዙትና በሚዲያ ዙሪያ ድል ተመዘገበ፥ Nigussu Tilahun አቶ ንጉሱ ጥላሁን በጭንቅላቱ ላብ እያጠመቀው መንዜነቱን በእልህ አስመሰከረ፥ እሰይ መክት አማራ ተባለ።
ሳይታሰብ ሊውጧቸው ነው ሲባል ለማና አብይ ከቲም ገዱ ጋር ተመሳጥረው ወያኔን ሸበለሉት፥ ዶክተር አብይ ሹመት ነው፤ ወይስ ምርጫ በሚባል የሚያሻማ ቃል Prime Minister Dr. Abiy Ahmed ጠቅላይ ሚኒስቲር ሆኖ ቁጭ አለና ነገራት ሁሉ በወያኔ ላይ ድንገት ተገለባበጡ።
የወያኔ ጉጅሊዎች አቦይ ስብሃትና አባይ ዲቃሎቻቸውን ይዘው ከፖለቲካው ጨዋታ ውጭ ሊሆኑ ስንዝር ቀርቷቸዋል፥ በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ ባህርዳር ላይ አይተውት የማያውቁት ውርደት ገጥሟቸው ለጌታቸው አሰፋ ስሞታ ሊናገሩ ወደ አዲስ አበባ መሄዳቸው ተሰምቷል።
ከዚያ በኋላ እየተከሰተ ያለው ነገር ቅጽበታዊ ነው፥ ትግሉ በይፋ ተጀመረ፥ የጥሎ ማለፍ ጨዋታው አገር ውስጥ ገባ፥ ታዋቂ ነን የሚሉ ድርጅቶች የጫጉላ ጊዜያቸው አለፈ፥በተለይ በውጭ የሚገኙት በሆነ ባልሆነው ሰበር ዜና ማስወራት ቀረና የሚያራግበው ሰው ቀነሰ፥ እውነቱ ግን ተቃዋሚው የሚያደርገውን ትግል አቁሞ ሳይሆን አገር ውስጥ በሚደረገው ግብግብ ቀልቡ ስለ ተያዘና ስራውን ወደዛ ስላደረገ ብቻ ነው።
ታዲያ እሄን ከውስጥ የተጀመረ የለውጥ ሂደት ተከትሎ ትግል ቀዘቀዘ፥ ለውጡ ተፋዘዘ፥ የሚሉ አንዳንድ ወገኖች በምናይበት ጊዜ፥ እነዚህ ሰዎች አንድም እኛ ያላማሰልነው ወጥ አይወጥወጥ በሚል የእኔነት አባዜ ተለክፈዋል፥ ወይም የፖለቲካን ሀ. ሁ.... አልተገነዘቡም በሚል እሄን ለማለት ተገደድን።
ፖለቲካ ተለዋዋጭ ነው፥ ፖለቲካ ሰጥቶ የመቀበል ተክህኖ የሚጠይቅ ጨዋታ ነው፥ የፖለቲካ ጉዞ እንደ ሁኔታው የትግል ስትራቴጅ እያወጣህ የምታስኬደው ፈጣን ነገር እንጂ እንደ ኃይማኖት አንድ ቦታ ግትር ብለህ ቆመህ የምትጠብቅበት የቁልቁለት መንገድ አይደለም ይላሉ ሙያውን ያጠኑ ሰዎች።
ነገር ሳላበዛ በምሳሌ ላስረዳና ላብቃ፥
አንዳንድ ጊዜ ዲል ያለ ሰርግ ተደግሶላቸው ያገቡ ሴቶች፥ በተለያየ ምክንያት መውለድ ላይ ይዘገያሉ፥ ታዲያ በትዳር ህይወታቸው የሚናገሩት አዲስ ነገር ገና ስላላፈሩ፥ ሰዎች በተዳሩ ቁጥር ስለራሳቸው ሰርግና ምላሽ እያሰቡ፥ ሌላውም ስለ እነርሱ ሙሽርነት ብቻ እንዲያወራ ይፈልጋሉ፥ እንዲያውም የእነርሱ ስም ካልተጠራማ ሰርግ በእኛ ጊዜ ቀረ አይነት ወሬ ይዘው የአዲሶቹን ሰርገኞች ፌስታና ድግስ በማናናቅና፥ ሙሽሮችን በማሸማቀቅ ተጽዕኖ ለመፍጠር ይሞክራሉ።
ሰሞኑን በተቃዋሚው ጎራ እየተሰማ ያለው ትግሉ ቀዘቀዘ የለውጥ ሂደቱ ተፋዘዘ ማለት ከዚህ የተለየ አይደለም። በተለይም ድምጻቸው ጎልቶ ይሰማላቸው በነበሩ የውጭ ሚዲያዎችና ዳያስፖራ ተቃዋሚዎች ተዘውትሮ ይነሳል።
ሲጀመር ትግል ይቁም ያለ ማንም ሰው የለም፥ በዚህም ሆነ በዚያ ያሉ ሰዎች ይቁም ቢሉም የህዝብ ጥያቄ እስካልተመለሰ ድረስ፥ የትግል ስልቱ ይቀያየራል እንጂ ጨርሶ ሊቆም አይችልም።
አሁንም ትግሉ ከዳር አገር ወደ መሃል አገር ገባ እንጂ አልቆመም፥ የኢትዮጵያ ህዝብ ከመቼውም በላይ እየታገለ ነው።
ታላቋ ሮም በአንድ ቀን አልተገነባችም፥ የሺህ ማይል መንገድ በአንድ ይጀመራል እንደምሉት
እንዲያ በዳዴ የጀመሩት ትግል ዛሬ ላይ ደርሷል፥ የዶክተር አብይ መንግስት ፈተናውን በአሸናፊነት ይወጣል ወይስ ይወድቃል በሂደት የሚታይ ነገር ነው።
እኛ ግን ለኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት እየተመኘን የአማራን ህዝብ እናደራጃለን፥ ትግላችን እንቀጥላለን።
ቲም ገዱ አንዳርጋቸው የቲም ለማን ድል በወያኔ ኢሕአዴግ ላይ እንዲደግም በማንኛውም መልኩ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን የለውጥ ጉዞ እያበረታታን ለስር ነቀል ለውጥ እንታገል። ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል፥
አማራ ሆይ መክት!
ኢትዮጵያችን ለዘላለም ትኑር። Tiruneh Yirga

የአማራ ብሔርተኝነት ወግ በቤተ መንግሥት

የአማራ ብሔርተኝነት ወግ በቤተ መንግሥት

በአማራ ክልል ከሚገኙ ዞኖች የተጠሩ በርካታ ሰዎች ታድመዋል፡፡ ከአዲስ አበባም በጣት የሚቆጠሩ አማራዎችም ተገኝተዋል፡፡ አመሻሹ 11፡30 ላይ ከታችኛው ቤተ መንግሥት (ኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት) ተገኘን፡፡ 12፡00 ገደማ ላይ በቤተ መንግሥቱ የእንግዳ መቀበያ የተለያዩ መጠጦች ለሚፈልግ ሰው ይሰጡ ነበር፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ጃንሆይ (ዐጼ ኃይለ ሥላሴ) ግብር ከሚያበሉበት አዳራሽ ገብተን ታደምን፡፡
በጣት ከሚቆጠሩ ደቂቃዎች በኋላ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ (ዶ/ር አቢይ አህመድ)፣ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ (አቶ ደመቀ መኮንን)፣የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ( አቶ ብናልፍ አንዷለም)፣የክልሉ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ወደ መድረኩ መጡ፡፡
በመቀጠል አቶ ንግሡ ስለፕሮግራሙ በማስተዋወቅ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ የምግቢያ ንግግር እንዲያደርጉ ጋበዟቸው፡፡
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የመግቢያ ንግግር በአጭሩ፤

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ አንድነት፣ ስለ ፍቅር፣ይቅር ስለመባባል ጠቀሜታና ፋይዳ ሰፋ ያለ ንግግር አደረጉ፡፡ በተለይ ስለይቅርታ ሁለት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ አንደኛው የደርግ ባለሥልጣናትን የሚመለከት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በውጭ አገር የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ነው፡፡
እንደ እሳቸው ገለጻ ወደ 23, 000 የሚደርስ ቁጥር ከቀይ ሽብር እና ደርግ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያን ጥሎ የተሰደደ ወይም በውጭ አገር የሚኖር ኢትዮጵያ አለ፡፡ ይቅር ተባብለን አገራቸው ገብተው በሰላም መኖር አለባቸው አሉ፡፡ የቀድሞው ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያምንም ይቀርታ አድርገንላቸው አገራቸው መጥተው መኖር አለባቸው አሉ፡፡
ስለ ሲኖዶሱ ሲናገሩም ፓትርያኩን አቡነ ማትያስን እንዳገኟቸውና ውጭ ስላለው ሲደኖዶስ እንዳወያይዋቸው፤ ሰላም ወርዶ አንድ ሆነው ጠንካራ ቤተ ክርስቲያን እንድትኖር ምኞታቸው እንደሆነ እንደገለጹላቸው ተናግረዋል፡፡
በመቀጠል በተለይ የብሔርተኝነትን ነገር ሲያነሱ ባልተቤታቸውን (ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽን) ምሳሌ በማድረግ ጉዳዩን ማብራራት ቀጠሉ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ በዚህ የእራት ግብዣ ላይ ቀዳማዊት እመቤቷ ታድመዋል፡፡ ሌሎች ግብዣዎች ላይ እንዳልተገኙ ገልጸው የዕለቱ ግብዣ ግን የአማራዎች እንደሆነ ሲነገራቸው እንደመጡ ተናገሩ፡፡ ይህንን ሲናገሩ እኛ አጨበጨብን፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን የሚያስጨበጭብ አይደለም አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለፍቅር፣ስለአንድነት፣ስለይቅርባይነት በርካታ ቁምነገሮችን አካፈሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረው እንደጨረሱ አቶ ንጉሡ መድሩኩን እንዲመሩ ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ጋበዙ፡፡ ዳንኤልም መጠነኛ ንግግር አድረጎ ውይይቱን በመምራት ለተለያዩ ሰዎች ዕድል ሠጡ፡፡
የእለቱ ሁለት ዓይነት ታዳሚዎች፤
=============
ታዳሚ አንድ-ኢትዮጵያዊያኖቹ ብቻ
---------------
ያው እንደተለመደው በርካታ አባቶቻቸችን እና እናቶቻችን አማራ የሚታወቅበትን የኢትዮጵያዊነት ባህርይ አስተጋብተዋል፡፡ አንዳንድ ወጣቶችም በተመሳሳይ በዚሁ መንገድ ተጉዘዋል፡፡ ስለ ልማትና ተያያዥ ጉዳዮች አንስተዋል፡፡
ታዳሚ ሁለት-አማራየሆኑ ኢትዮጵያዊያኖቹ፤
---------------------------
በዚህ ምድብ ሥር የሚካተቱት ስለአማራ ብሔርተኝነት መንስኤውም ግቡም ከኢትዮጵያዊነት ጋር ስላለው ግንኙነትም አብራርተዋል፡፡ አስረድተዋል፡፡ የአማራ ብሔርተኝነት የተወለደው በበደል፣በመከፋት፣በመገፋት ነው፡፡ እንኳንስ ለኢትዮጵያ ለመላው ጥቁር ሕዝብ መኩሪያ በሆነው ታሪኩ እንዲያፍርበት ተሠራ፡፡ እምዬ ምኒልክን ያህል መሪ ስም መጥራት እንኳን እንዲያሸማቅቅ ተደረገ፡፡ አማራ አገር ቢያቀና ነፍጠኛ ተባለ፡፡ ኢትዮጵያዊ ነኝ ሲል ማን ኢትዮጵያዊ ያልሆነ አለ ተብሎ ትምክህተኛ ተባለ፡፡ በተለይ በሁለተኛው ሚኒሊየም (ከ1000-2000 ) በተካነወኑ የአማራ ታሪኮች አማራ እንዲያፍር ሌት ተቀን ተሠራ፡፡ ቀና እንዳይል በሚያሸቅቅ ሁኔታ ደባ እና በደል እተሠራበት፡፡ በመሆኑም ከታሪኩም ከባህሉም እንዲነጠል በተደራጀ መንገድ ተዘመተበት፡፡
ከኢኮኖሚውም እንዴት እንደተነጠ እና እንደተበደለ በርካታ ማነጻጸሪዎች እየቀረቡ አስተያየት ተሠጠ፡፡ ለአብነትም በኢትዮጵያ ካሉ ደረጃ አንድ ኮንትራክተሮች ውስጥ እንደው ስም ያለው አንድ ኮንትራክተር አለን? የሚል ጥያቄያዊ ትችት ቀረበ፡፡ ከኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካውም የደረሰበበትን መገለል ተነግሯል፡፡ በመሆኑም የአማራ ብሔርተኝነትን የፈጠረው ከ1983 ዓ.ም. በኋላ የደረሰበት በደል እንደሆነ በበርካታ ወንድምና እህቶች ተብራርቷል፡፡ (የአንዳንዶቹን ስም ያልገለጽኩት ያው በሚታወቅ ምክንያት ነው፡፡ )
የአማራ ብሔርተኝነት ለማንም ስጋት እንደማይሆን በተለይ ዶ/ር ሲሳይ መንግሥቴ አብራርተዋል፡፡ ሕወሃት ስትመሠረት ጠላት አብጅታ ነው፡፡ አማራን ጠላት አድረጋ፡፡ የአማራ ብሔርተኝነት ግን ማንንም በጠላትነት አልሳለም፡፡ ራሱን ለመከላከል እንጂ፡፡ (ነገሩ ያው የመክት ጉዳይ ነው!) አማራ መቼም ቢሆን መቼም በኢትዮጵያዊነት አይደራደርም፡፡ ነገር ግን አማራ ደግሞ ላይመለስ አማራ ሆኗል፤ አማራ ነው፡፡ በመሆኑም የአማራ ብሔርተኝነት ለማንም ስጋት እንዳልሆነ ተብራርቷል፡፡
አብሮ በመድረኩ የተነሳው አማራ ክልልም ሆነ ብአዴን፣ ጸረ አማራ ወይም አማራ ጠል ከሆኑ አማራሮች እንዲላቀቅ ነው፡፡ እነዚህ አማራን የሚጠሉ ጸረ አማራ አመራሮች አማራን በመምራትም ሆነ እንደ ጆፌ አሞራ ሌሎችን በመዞርና አማራን በማጥቃት መቀጠል እንደሌለባቸውም ተወስቷል፡፡
በተለይ ከየክልሉ የሚፈናቀሉ አማራዎች ጉዳይ በዚህ ምሽትም ትኩረት ተሰጥቶበታል፡፡ ብጹእ አባታችን አቡነ አብርሃም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
የወሎ ቴሪሸሪኬር ሆስፒታልም ብዙ ሰው ከተናገረበት ጉዳይ አንዱ ነበር፡፡ ከከሚሴና አካባቢዋ የታደሙት አባቶች በአሸባሪነት ተከሰው ስለደረሰባቸው ግፍ ( ሽንት ሁሉ ይሸናባቸው እንደነበር) ሁሉንም ሰው ወደ ሐዘን ድባብ በከተተ ሁኔታ ተናግረዋል፡፡ ከሰሜን ወሎ የመጡ አንድ ጎልማሳም ስለወልዲያ፣ቆቦና መርሳ ሁኔታ ተናግረዋል፡፡ ሼክ አሊ አላሙዲንንም ለማስፈታት እንዲሞክሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዝጊያ ንግግራቸው፤
===============
በታወቀው ንግግር አዋቂነታቸው እና በበርካታ ምሳሌዎች አሁንም ስለመተባበር፣ስለ አንድነት፣ ስለ ይቅር ባይነት በተለይም እምዬ ምኒልክን በምሳሌነት በማንሳት አስረድተዋል፡፡ የንጉሥ ተክለሃይማኖትና የእምዬን ታሪክ አውስተዋል፡፡ ማርከው የሚያክሙ እንዲሁም የሚሾሙ መሆናቸውን እና ይቅር ባይነታቸውን በአርያነት አንስተው አስረድተዋል፡፡
በመጋረጃ የተሸፋፈነውን የጃንሆይን ዙፋን አስከፍተው መኩሪያችን እንደሆነ፣ከመስከረም ጀምሮ ለሕዝብ ክፍት እንደሚሆን ሁሉ ተናገሩ፡፡ ላይኛው ቤተ መንግሥትንም (የምኒሊክ ቤተ መንግሥትንም)አስደናቂነት እና ሁላችንም የየድርሻችንን መወጣት እንዳለብን ተናግረዋል፡፡
የወሎ ቴሪሸሪ ኬር ሆስፒታልንም ከአቶ ደመቀ ጋር እንደተነጋገሩ እና ትኩረት እንደሚሰጡበት ተናግረዋል፡፡
የሼክ አሊ አላሙዲን ጉዳይንና ሌሎች በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ እሰረኞችን በሚመለከት ለመወያየት የፊተችን ሐሙስ ወደ ሳዑዲ እንደሚሔዱ ነግረውናል፡፡
ሦስት የመውጪያ ወጎች፤
========
አንድ
-----
አንዳንድ ሰዎች፣በዚሁ መድረክም ጭምር፣ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ ቦታዎች መዟዟር እና መንቀሳቀስ ስላበዙ ጊዜ እንስጣቸው፤አሁን በየቦታው ቢዞሩም ቢሮ ሆነው ሥራ ባይሰሩም የሚል አንድምታ ያለው ንግግር ስለበዛ ይመስላል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መደበኛ ሥራቸውን እና ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮችን እንደውም ከወትሮው በበለጠ ሁኔታ እየሠሩ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ሁለት፤
------
ጠቅላዩ በዚሁ ግብር ላይም ጭምር እንደታየው ስለደረሰ በደል ስለተወራ እሳቸውም ብዙዎቻችን ተበድለናል አሉ፡፡ ለዚህም ደግሞ ፊታቸው ላይ የወጣውን ማድያት አሳዩን፡፡ ስለማዲያቱ ሁኔታ ይምታውቀው ባልተቤታቸው እንደሆነችም ተናገሩ፡፡
( ይቺን ነገር ለታዳሚው ከመናገራቸው በፊት በእራት ሰዓት እኔና ጓደኞቼ (ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣አንዷለም አባተ/የአጸዴ ልጅ፣ምንዳራለው ዘውዴ፣ዶ/ር ሰጥአርጋቸው) ወደተቀመጥንበት መጥው ስለነበር የእኔን እጅ ይዝው ፊታቸውን አሳዩኝ፡፡) ፊቴን ማድያት በማዲያት እንዲሆን ያደረጉትን ልበቀል ብል ስንት ሰው ማሰር አለብኝ? አሉ፡፡ በመበቃቀል ፍቅር አይገነባም አሉ፡፡
ሦስት፤
------
የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር የአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ስም በብዙ ሰዎች በበጎ ተነስቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም እንዲህ አሉ፡፡ ሰዎች ብዙ ጊዜ በአድናቆት የሚናገሩት ስለ አቶ ገዱና አቶ ለማ መገርሳ እንዲሁም አልፎ አልፎ ስለ እኔ ነው አሉ፡፡ ነገር ግን መርሳት የሌለባችሁ ከእኛ ጀርባ አንድ ሰው ያሉ መሆናቸውን ነው አሉ፡፡ እሳቸውም አቶ ደመቀ መኮንን ናቸው አሉ፡፡
በሉ ደህና እደሩ፡፡ ከምሽቱ 4፡30 አካባቢ ውይይቱ ተጠናቀቀ፡፡ እኔም ሌሊት ጻፍኩት፡፡ ለቴሌቪዥንም ይሁን ለሬዲዮ ቀረጻ አልተደረገም፡፡ ሞባይልም ካሜራም የለም፡፡"
(ውብሸት ሙላት)

Tuesday, February 6, 2018

“በአባቶቻችን ተጋድሎ የተገነባችውን ኢትዮጵያ እኛም አስውበንና አንድነቷን አስጠብቀን ለቀጣይ ትዉልድ የማሻገር ታርካዊ ኃላፍነት አለብን”

“በአባቶቻችን ተጋድሎ የተገነባችውን ኢትዮጵያ እኛም አስውበንና አንድነቷን አስጠብቀን ለቀጣይ ትዉልድ የማሻገር ታርካዊ ኃላፍነት አለብን” ከኦሕዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ
ከኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ
[OBN 29 05 2010]
የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ) ማዕከላዊ ኮሚቴ የተጀመረው የለውጥ ጉዞና የወደፊት አቅጣጫ ለ10 ቀናት ዝርዝር ግምገማ በማድረግ ዛሬ ማምሻዉን በስኬት አጠናቋል፡፡ ግንባራችን ኢህአዴግም በጥልቅ ለመታደስ የጀመረውን ንቅናቄ ዳር ለማድረስ በቅርቡ ራሱን ገምግሞ አቅጣጫ ማስቀመጡ የሚታወስ ሲሆን ከግምገማው በመነሳትም ሀገራችን ኢትዮጵያና ክልላችን በፖለቲካዊ፤ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስኮች ያለችበትን ሁኔታ በዝርዝር በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
አስር ቀናት በፈጀው የአሁኑ ውይይታችን፣ የሕዝባችን ሰላምና አብሮነት በምንም መልኩ አደጋ ውስጥ እንዳይገባ የክልላችን ሕዝቦች እና መሪ ድርጅቱ ኦህዴድ በቅንጅት በመስራት የሀገራችንን ሕልውና መታደግና የተጀመረውን የለዉጥ ጉዞ በስኬት እንዲጠናቀቅ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን አጽንኦት ሰጥቶ ተወያይቷል፡፡ድርጅታችን ከሚታወቅባቸው መለያ ባህሪያቱ እያንደንዱ ጉድለቶቹን ያለማመንታት መቀበልና ለማረም ጥረት ማድረግ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ የዴሞክራሲያዊ ድርጅት ባህሪይ በመሆኑ ከሕዝብ የሚነሱ ቅሬታዎችን ማድመጥ፣ ሕዝቡን ከልብ ይቅርታ የመጠየቅና የእርምት እርምጃ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን በዝርዝር በመምከር አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
የፌዴራል ስርዓቱን አደጋ ውስጥ ሊጥሉ የሚችሉ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ምክንያቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለይቶ አፋጣኝ እርምጃዎችን በመውሰድ የሕዝቡን መሻት ማሳካት ለነገ የማይባል ጉዳይ መሆኑን በዝርዝርተመልክቷል፡፡ ፍትሃዊ የኃብት ክፍፍል፣ አሳታፊ የፖለቲካ ስርዓት፣ ሰላምና ፍትህ እንዲሰፍን በጥብቅ ዲስፒሊን በመስራት የሕዝብ እርካታን ማረጋገጥ ጊዜ የማይሰጠው መሰረታዊ አጀንዳ ስለመሆኑ መክሯል፡፡ የኦሮሞ ሕዝብ ከመላዉ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር በመተባበር የሀገራችንን ቀጣይ ጉዞ የማቅናት ሚናውን ዛሬም እንደትላንቱ መጫወት እንደሚገባውም ተወያይቷል፡፡
በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መካከል ያለውን ግንኙነት በዴሞክራሲ አግባብ በማጠናከር የጋራ አላማችንን ለማሳካት ርብርብ ማድረግና የሀገሪቱን ሕልውና ከአደጋ መከላከል እንደሚገባ በዝርዝር በመምከር አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
የፌዴራላዊ ስርዓታችንን አደጋ ላይ የጣሉ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን፣ ሕዝቡ በመሪ ድርጅቱ ላይ እንዲያምጽ ያስቻሉ የመልካም አስተዳደር እጦቶችን፤ስልጣን ህዝብን ማገልገያ መሳሪያ መሆኑንበመዘንጋትበርስትነት ይዞ ለግል ምቾትና ጥቅም ቅድሚያ መስጠትን፣ በነጻነት ተዘዋውሮ የመስራት መብትንነፍጎ በመቶ ሺህዎችየሚቆጠሩ ሕዝቦችንእስከማፈናቀል የደረሰ ድርጊትን፤ በኢንቨስትመንት ስም የመንግስትና የህዝብ መሬት መመዝበሩን፤እንዲሁም የሕዝቦች ሰላምና ጸጥታ መደፍረሱን እና የመሳሰሉትንእየተፈጸሙ ያሉ አደገኛ ድርጊቶችን ሕዝቡን ባሳተፈ መልኩ አምርሮ በመታገል የሀገራችንን ሕልውና መታደግ ልዩ ትኩረት የሚሹ አበይት ጉዳዮች መሆናቸውን በዝርዝር ተመክሮባቸዋል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተከሰቱ ግጭቶች የበርካታ ዜጎች ሕይወት ጠፍቷል፤ ንብረት ወድሟል፤የሕዝቦች በሰላም ዉሎ ማዳር፣ ወጥቶ መግባት ከፍተኛ ስጋት ላይ ወድቃል፡፡ለእነዚህ ችግሮች መከሰት ኃላፊነቱን ወስዶእርማት ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ አጽንኦት ሰጥቶ በመምከር አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
የፌዴራል ስርዓቱን አደጋ ላይ በመጣል ግላዊና ቡድናዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ በንጹሃን ዜጎች ሕይወት ላይ አደጋ ያደረሱና በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅ ፀያፍ ድርጊቶችን የፈጸሙ ኃይሎች በሕግ እንዲጠየቁ ለማድረግ፣ እንዲሁም መሰል ስህተት እንዳይደገምና የሕግ የበላይነት በመላ ሀገሪቱ እንዲሰፍን ለማስቻል ሕዝቦችንን በማሳተፍ ትግሉን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር የግድ መሆኑን ከግንዛቤ አስገብቶ ማዕከላዊ ኮሚቴው አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
ቀንደኛ የሕልውናችን ጠላት ድህነት መሆኑ ቢታወቅም ይህንን ጠላት ለመዋጋት በመንግስት፣ ድርጅትና ሕዝብ ትስስር ሊሰራ እንደሚገባውና አዳዲስ ሃሳቦችን አያፈለቀ አመራር የመስጠት ጉዳይ ከድርጅታችን እንደሚጠበቅ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
ኃብት ማመንጨት ብቻ ሳይሆን ፍትሃዊ የኃብት ክፍፍል እንዲኖር ማስቻል፣የኃብት አጠቃቀምንም ከብክነት የጸዳ ማድረግ፣ ግልጸኝነትና ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ አሰራር በማስፈን ሕዝቡ እንዲያለማ ከማስቻል በዘለለ የመቆጣጠር ሚናውንም ከፍ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
አዳጊ ኢኮኖሚን የሚያንኮታኩቱ መጥፎ ልማዶችን በተለይም ሙስና፣ ኮንትሮባንድ፣ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ፍላጎቱን ማኮላሸት፣የአቅርቦት ሰንሰለቱን ማስተጓጎል፣ ማንኛምውም የገበያ ፍትሃዊነትን የሚያዛቡ አሉታዊ ተግባራትንአጥፍቶ በምትኩ በዘመናዊነት የታገዘ ፍትሃዊ አሰራርን መዘርጋት፣ ያልተገባ የጥቅም ትስስር ያላቸዉን ሰንሰለቶች በጥናት ላይ በመመሰረት የመበጣጠስ ተግባር በተቀናጀና የሪፎረም ሥራውንበሚያሳልጥ መልኩ እንደሚፈፀም አቅጣጫ ተቀምጠዋል፡፡
ሕገመንግስታዊ ድንጋጌዎች ሳይሸራረፉ ተግባር ላይ እንዲውሉ፣ የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ ዜጎች ካለምንም ስጋት ከቦታ ቦታ ተዘዋውረው እንዲሰሩ በማስቻል በፍትህ ስርዓቱና በፖሊሲ ስርዓታችን ላይ ተጨባጭ ለውጥ ሊያስገኙ የሚችሉ ሁለንተናዊ ሪፎርም ማከናወን እንደሚገባ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
ከክልሎች ጋር የጀመርነዉን ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ህግ መንግስታዊነቱን ጠብቆ እንዲቀጥልና ፌዴራላዊ ስርዓታችን ይበልጥ መጠናከር የሚችልበት ሁኔታ አጽንኦት ተሰጥቶት ተመክሮበታል፡፡የኦሮሞ ሕዝብ የመቻቻል፤የመደጋገፍና አብሮ መኖር እሴቶችን ያዳበረ በመሆኑ ከሌሎች ሕዝቦች ጋር በመከባበርና በፍቅር አብሮ በመኖር የሁሉም ዜጎች መብት በእኩል እንዲከበር ከወንድም ሕዝቦች ጋር አብሮ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ ጥላቻን በጥላቻ፣ክፉተግባርን በሌላ ያልተገባ ድርጊት መመከትሊቆም ይገባዋል፡፡ በመሆኑም ተከሰቱ ለሚባሉ ችግሮች ሁሉ መፍትሄው ፍትሃዊና ሕጋዊ የትግል ስልትን መከተል መሆኑ ታምኖበት ከጥፋት ተግባራት በመታቀብኦሮሙማን በሚያጎላአቃፊ መሆን እንደሚገባ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ሕዝቦች ጋር የነበረንን መልካም ግንኙነት በመመለስ እንደ ወንድማማች ሕዝቦች የባይተዋርነት ስሜት እንዳይፈጠር በሚያስችል መልኩ በታላቅ የኃላፊነትስሜት እንዲመራግዚያዊ ችግሮችን ፈተን ለዘላቂ የጋራ ጥቅሞቻችን በወንድማማችነት መንፈስ እነድንረባረብ የሶማሌም ይሁን ሌሎች ብህረ ብሄረሰቦች በኦሮሞ ባህልና የገዳ ስርዓተ ባስተማረን መልኩ በፍቅርና በአብሮነት እንዲኖሩ ለማስቻል ሕዝቡ የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ማዕከላዊ ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል፡፡
የሐሳብ ልዩነቶችን ማጥፋት አስቸጋሪ እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ስለሆነም ሁል ጊዜ ለውይይትና ለክርክር አውድ ማስፋት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል፡፡ ፍላጎትን በውይይት እንጂ በኃይል የማስረጽ ዝንባሌ እንዳይታይ በቀጣይነት መስራት እንደሚያስፈልግም መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
ዛሬ አድገው የሀገራቸውን ህዝብ ኑሮ በከፍተኛ ደረጃ ያሻሻሉ ሀገራት ታሪክ ሲመረመር በአገራዊ ጉዟቸውውስጥ ሕዝባዊ አመጽን ያስተናገዱ፣የወጣቶች ቁጣ የደረሰባቸውና መሰል አጋጣሚዎችን በዴሞክራሲያዊ መንገድ መቀልበስ የቻሉትየዘላቂ ልማት ባለቤት እንደሆኑ ታሪካቸው ያሳያል፡፡ በመሆኑም በወጣቶች ላይ የሚታየውንፍትህ የመሻት ቁጣሀገርን በማያፈርስ መልኩ ከሃይል በፀዳ ሁኔታ ሰላማዊ የትግል ስልት እንዲከተሉ በማስተማር የዴሞክራሲ ባህልን ማዳበር አስፈላጊ መሆኑን ኮሚቴው ያምናል፡፡ ዋነኛ ሚናውም የተሻለች ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ማሸጋገር በመሆኑ የተሻለች ሀገር ብቻ ሳይሆን ብቁ ተረካቢ ወጣቶችንማፍራት እንደሆነም ይገነዘባል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለው ድርቅ፣ ግጭት፣ስደት፣ የሕዝብ መብዛትያልተደራጀ ኢኮኖሚና ያልደበረ የዲሞከራሲ ባህል ባለበት ሀገርነገሮች እንዲባባሱ ከማድረግ አልፎ የሀገር ህልውናን አደጋ ውስጥ እስከመጣል እንደሚደርስ ታውቆየተሻለች ሀገር የመፍጠሩና ብዙ ተረካቢ የማፍራቱ ተግባር በጥንቃቄና በኃላፊነት ስሜት እንዲከወን በዝርዝር ተመክሯል፡፡
ይህንንም ከማሳካት አኳያ ቅድሚያ ከተሰጣቸው ተግባራት መካከል ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተፈናቀሉ ወገኖችን ከጊዜያዊ መጠለያ ወደ ቋሚ ቦታ ማስፈር፤የወጣቶችን የስራ አጥነትን በመቀነስ የኑሮ ሁኔታቸውን ማሻሻል፤ የመልካም አስተዳደርና ብልሹ አሰራሮችን ማስተካከል፤የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ማዘመን፤ፍርድ ቤት፣አቃቤህግ፣ፖሊስ፣ የወረዳና የቀበሌ መዋቅሮችን መልሶ ማደረጀት፤ሰላምና ፀጥታ በማስከበር የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ ይገኙበታል፡፡
በመላ የሀገራችን ህዝቦች ይሁንታ አፋን ኦሮሞ የፌዴራል የስራ ቋንቋ እንዲሆንድርጅታችን ይሰራል፡፡ በተጨማሪም በሂደት ላይ ያሉና ያልተጠናቀቁ መሰረታዊ የህዝብ ጥያቂዎች በጥብቅ ዲስፕልን እዲፈጸሙ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
በድርጅቱተጠያቅነትን ለማረጋገጥ፤መድረኩ የሚጠይቀውን የትግል ልክ በብቃት ለመፈፀም፣ በቀጣይም ጥንካሬውን አጎልብቶ መጓዝ ይችል ዘንድ 14የኢህአዴግ ምክር ቤት አባላት እንዲተኩ እና4 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትም እሰከሚቀጥለው ጉባኤ እንዲታገዱና አንድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በማስጠንቂያ እንድታለፍ የወሰነ ሲሆን የዉስጠ ድርጅት ዲሞክራሲ የማስፋትና የአመራሩን የሃሳብና የተግባረ አንድነት ይበልጥ ማጠናከር በቀጠይነት እዲሰራበት ተመክሮዋል፡፡
የተከበርከው የኦሮሞ ሕዝብ
================================
ለዘመናት ትከሻህ ላይ ተጭኖ የነበረውን የጭቆና ቀንበር ለመስበር ሁልጊዜም ታሪክ እየዘከረው የሚኖር አኩሪመስዋዕትነት ከፍለሃል፡፡ በከፈልከው መስዋዕትነት ከሌሎች ወንድሞችህ ጋር በመሆን አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመፍጠር፤ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲና ሁሉን አቀፍ መብቶች የተረጋገጡባትን የበለፀገች ሀገር ለመገንባት መሰረት ጥለሃል፡፡ በተጀመረው የግንባታ ሂደት ውስጥ የመጡ ተስፋ ሰጪ ድሎች እንዳሉ ሁሉ የጭቆና መሰረት የሆኑ አስተሳሰቦችና አሰራሮችን የሚፈጥሩ አዝማሚያዎችም ይታያሉ፡፡ በነዚህ አዝማሚያዎች ላይም የጀመርከውን ትግል አጠናክረህ መቀጠል ያንተም ሆነ የወንድም ሕዝቦች የሕልውና ጉዳይ ነው፡፡
የመደብ ጭቆና ምን ያህል አስከፊ እንደሆና አዎንታዊ ለውጥን እንደሚገታ ባለፈው ታሪክህ ካንተ በላይ የሚገነዘብ የለም፡፡ በአሁኑም ሰዓት ተመሳሳይ መደባዊ ጭቆና ዳግም በሀገራችን እንዳያቆጠቁጥ ትግልህን አጠንክረህ መቀጠል ይገባሃል፡፡
በሁሉም የታሪክ ምዕራፎች ኢፍትሃዊነትና ጭቆናን ባለመቀበል ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በመሆን መስዋዕትነትእየከፈልክ ወደ ድል ስትራመድ እንደነበረው ሁሉ አሁንም ሀገራችንን የገጠሟትን ፈተናዎች በታጠቅከው የገዳ ስርዓት ቱባ ባሕል መሰረት ብሄር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን በማቀፍና ከጎንህ በማሰለፍ ትግሉን ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የአዲሲቷን ኢትዮጵያ ህልውና በማስጠበቅ ለውጧን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ የማስቀጠል ኃላፊነትህን እንዲትወጣ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የኦሮሚያ ክልል ወጣቶች
የክልላችንም ሆነ ሀገራዊ ለውጦች ያለወጣቱ ተሳትፎና መሪነት የሚታሰብ አይደለም፡፡ በዚሁ መሰረት እስካሁን በሀገራችን የመጡ ለውጦች በወጣቱ ተሳትፎና አኩሪ መስዋዕትነት የመጡ መሆናቸውን ኦህዴድ ይገነዘበዋል፡፡ ወጣቶቻችን በሁሉም መስክ የተጀመሩ የለውጥ እንቅስቃሴና መልካም ጅምሮች ወደ ላቀ ድል እንዲሸጋገሩ በባለቤትነት መሳተፍና ኃላፊነትን መወጣት፣ይህንንም በተደራጀ መልኩ መተግበር ይገባዋል፡፡ ወጣቱ በሁሉም መስክ የሚያደርገውን ትግል ምክንያታዊና ሳይንሳዊ በሆኑ ሃሳቦች እየተመራ፤ ዴሞክራሲያዊነትን በጠበቀና ተደማሪ ለውጦችን በተንከባከበ መልኩ የሁሉም መብት ተከብሮ፣ የሀገራችንም ህልውናና የክልላችን ሰላምእንደተጠበቀ የሚቀጥልበት አካሄድ እንዲረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ድርጅታችን ኦህዴድ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የኦሮሞ ምሁራን
================================
በሁሉም የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኦሮሞ ሕዝብ ባለፈበትየትግል ሂደት ውስጥ እናንተም መስዋዕትነት ከፍላችኋል፡፡ አሁንም በደረስንብት የትግል ምዕራፍ ውስጥ ከሕዝባችሁና ከመሪው ድርጅታችሁ ኦህዴድ ጋር በመሰለፍ ዋንኛው ሥራ የሆነውን ሃሳብን የማፍለቅና የትግሉን አቅጣጫ በጥናትና በምርምር የማሳየት የማይተካ ሚናችሁን እንደሁል ጊዜው መወጣት ይኖርባችኋል፡፡ ድርጅታችን ኦህዴድ፣ ምሁራንን ባላቸው አደረጃጀትም ሆነ በግል ክህሎታቸው፣እውቀትና የአመራር ብቃትም ጭምር አብሮ ለመስራት የጀመረውን ሥራ በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል ወስኗል፡፡ በዚሁ መሰረት የተከበራችሁ የኦሮሞ ምሁራን የጀመራችሁትን ጠንካራና ተኪ የሌለው ሚናችሁን በመወጣት አጠናክራችሁ ትግሉን እንድትቀጥሉ፣ ለስኬትም እንድትረባረቡ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ሰራተኞች
================================
የኦሮሞ ሕዝብ ባደረገው ትግል የራሱን ክልል መስርቶ ያሉበትን ችግሮች ለመፍታትና ራዕዮቹን ለማሳካት ትልቅ የመንግስት መዋቅር ዘርግቷል፡፡ በዚህ መዋቅርውስጥ የሕዝባችንን ችግር መፍታት የሚቻለው ከእውቀትና ክህሎት በተጨማሪጠንካራ ዲሲፒሊን ባለው የመንግስት ሰራተኛ ነው፡፡ በመሆኑም፣በመንግስት መዋቅር ውስጥ እየፈጠረበት ያለውንየመብት ጥሰት፣ የመልካም አስተዳደር እጦት፣ እየተስፋፋ ያለው ሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነት፣ ኢ-ፍትሃዊነትና የዴሞክራሲ እጦት ችግሮችን ለመፍታትየክልላችን መንግስት ሰራተኞች ቁልፍ ሚና አላችሁ፡፡ሕዝባችንን አንገት ያስደፋውን ዋነኛ ችግሩንበመቅረፍ ብልጽግናን ለማስፈን፣ የማስፈፀም አቅምን ለማጎልበት፣ቀን ከሌሊት ተግታችሁ የመስራት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የኦሮሚያ ክልል የፀጥታ አካላት
================================
በክልላችን ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ ከሕዝባችን ጋር በተለይም ከወጣቶች ጋር በመቀናጀት የሕዝባችንን ጥቅምና ሀብት ሲዘርፉ የነበሩ ኮንትሮባንዲስቶች ላይ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ እንዲሁም በክልላችን የተጀመረውን ሪፎረም ለማደናቀፍ ዝርፊያ ድርጊታቸውን ማስቀጠል የሚፈልጉ የተደራጁ ኪራይ ሰብሳቢዎች የከፈቱትን ጥቃት ለመመከት በግንባር ቀደምነት ተሰልፋችሁ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍላችኋል፡፡ በዚሁም የአዲሲቷን ኢትዮጵያ ሕልውና እንዲቀጥል ድርሻችሁን በመወጣት ከአደጋ እየታደጋችሁ ትገኛላችሁ፡፡
የኪራይ ሰብሳቢዎች ቡድን በመንግስት ስልጣን የመክበር አባዜ ከስር ተነቅሎ፣ የሕግ የበላይነት ሰፍኖ እስኪሸነፍ ድረስ የጀመራችሁትን ትግል ሕዝብን በማሳተፍ በከፍተኛ ዲሲፒሊን ሕዝባዊ ኃላፊነታችሁን መወጣት ይገባችኋል፡፡ በክልላችን አስተማማኝ ሰላምና የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት፣ እንዲሁም ፍትህ የሰፈነበት እንዲሆንና ዜጎቻችን መብታቸውተከብሮ ስርዓት አልበኝነት እንዳይኖር የተሰጣችሁን ተቋማዊ ኃላፊነት ከሕዝብ ጋር በመቆም ሕዝባዊ በሆነ መንፈስ እንድትወጡ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የኦህዴድ አባላት
================================
ተንሰራፍቶ የቆየውን ጭቆና ለማስወገድ ሕዝባችን ሲያካሄድ በነበረውን መራራ ትግል ውስጥ የመርነት ሚናንተቀብለህ መስዋዕትነት በመክፈል የዛሬው ምዕራፍ ላይ እንዲደርስ የበኩልህን አስተዋፅኦ አበርክተሃል፡፡ ጠንካራ ድርጅት ያላ ጠንካራ አባል ሊታሰብ አይችልም፡፡ ኦህዴድ ያለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት እንዲወጣ አሁን በደረሰበት የትግል መድረክ የሚመጥን ቁመና እንዲኖረው ለማስቻልና ለማስቀጠል የድርጅታችን አባላት የድርጅታችሁን አላማ በጥብቅ ዲስፒሊን ለማሳካት ቀን ከሌሊት መታገል ይገባችኋል፡፡ ሕዝባችን በተለያየ ደረጃ እያደረገ ባለው ትግል ውስጥ አባሎቻችን በግንባር ቀደምነት በመሳተፍና በመምራት ችግሮችን በኃላፊነትመፍታት ይገባቸዋል፡፡ አሁን የደረስንበት የትግል ምዕራፍ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት በቅድሚያ በመክፈል ለሌሎች ምሳሌ በመሆን የድርጅታችሁን ተልዕኮ በተሰማራችሁበት መስክ ሁሉ በማሳካት የሕዝባችንን ጥያቄ በአፋጣኝ እየመለሰ፣ ትግሉን በግንባር ቀደምነት በመምራት አዲሲቷን ኢትዮጵያ እውን የማድረግ ኃላፊነቱን የሚወጣ፣ ጠንካራና ከለውጥ ጋር ራሱን የሚያሳድግ ድርጅት እውን እያደረጉ መጓዝትኩረት የሚሻ በመሆኑ ይህንንም በብቃት መወጣት ይገባችኋል፡፡
የተከበራችሁ በውጭ ሀገራት የምትኖሩ የኦሮሞ ተወላጆች
================================
በኦሮሞ ሕዝብ የለውጥ ጉዞ ውስጥ ባላችሁ እውቀትና ኃብት በተደራጀም ሆነ ባልተደራጀ መልኩ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ ለመወጣት ስታደርጉ የነበረውን ርብርብ የሚፈታተኑ ሁኔታዎች እንደነበሩ እና መድረኮችም አስቸጋሪ እንደነበሩ ኦህዴድ ይገነዘባል፡፡ በሕዝባችን አንድነትናሁለንተናዊ የለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂ፣ባላችሁ ተሞክሮዎና ትስስር፣ በኃብትና በመሳሰሉት ሁሉ እንድትሳተፉና የሕዝባችንን ችግር በጋራ እንድንፈታ፤ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎችም እንዲመቻቹ ኦህዴድ ጠንክሮ እንደሚሰራ ሊያረጋግጥ ይወዳል፡፡ በዚሁ መሰረት በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኦሮሞ ተወላጆች በሕዝባችን ጥቅም ላይ ያለምንም ድንበርና ልዩነት በጋራ እንድንሰራ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች
================================
ድርጅታችን ኢህአዴግ፣በሀገራችን ሕዝቦች ላይ የተጫነውን ጸረ-ዴሞክራሲ፣ ድህነት፣ የመልካም አስተዳደር እጦትና ኋላቀርነትን ለመፍታት ባደረገው እንቅስቃሴ ተስፋ ሰጪ ድሎችን ማስመዘገብ የጀመረው በውስጡ ያለውን ችግር በተከታታይ በመፈተሽና በመፍታት ላይ ነው፡፡ በቅርቡ በኢህአዴግ ደረጃ በተደረገ ግምገማ በእህት ድርጅቶቹ መካከል የተፈጠረው ያልተገባ ግንኙነትበሂደትም ወደ ጥቅም ቡድተኝነት እያደገ በመምጠቱ የነበረው ግንኙነት እያሻከረ እንዲሄድ አድረገዋል፡፡ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴም ጉዳዩን በጥልቀት በመገምገም ማንኛውም ግንኙነቶች መርህና መርህ ላይ ብቻ እንዲመሰረቱና ዴሞክራሲያዊ ትግልን ማዕከል ያደረጉ እንዲሆኑ ለማስቻል ትኩረት ሰጥቶ ተወያይቶበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ በዚሁ መሰረት የእህት ድርጅቶች አሁን በደረስንበት የትግል ምዕራፍ በግንባራችን ኢህአዴግ ተገምግመው አቅጣጫ የተቀመጠባቸውን ጉዳዮች ያለምንም መሸራረፍ እንዲፈፀሙና የሕዝባችንን ጥያቄ ለመመለስ ከመቼውም ጊዜ በላይ በአንድነት ርብርብ እንድናደርግ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች
================================
በብዝሃነት ለተገነባች ሀገራችን ኢትዮጵያ ዴሞክራሲ የህልዉና ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡ እንደ ነብር ዥንጉርጉር የሆነው የእርስ በእርስ ግንኙነታችን የሃሳብ ልዩነትን ማስተናገድ የሚያስችል አሰራርና ባህል ማዳበር ያስፈልገዋል፡፡ከሃይል የፀዳ፣ በዉይይትና በምክክር የሚያምን፣ ይበልጥ ለሀገር የሚበጅ ሃሳብ የሚፈልቅበት የውይይት ባህል እንዲዳብር የፖለቲካ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ ነው፡፡በዚህ ወሳኝ ወቅት የሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች አስተዋይነትና አርቆ አሳብነት የሚፈተንበት ጊዜ መሆኑ ግለፅ ነው፡፡ በመቀራርብና በመነጋገር የፖለቲካ ባህላችንን እንድናሻሽል ብሎም የሀገራችንን መፃኢ ዕድል በጋራ ማበጀት እንችል ዘንድ ተቀራርበን እንድንሰራ ድርጅታችን ይፈልጋል፡፡
ዴሞክራሲ ለሀገራችን ሕዝቦች የሕልውና ጉዳይ ነው፡፡ ዴሞክራሲ ለመገንባት የሀሳብ ልዩነቶች የሚስተናገዱበት ማዕቀፍና አሰራር እንዲሁም ባህልና አስተሳሰብ እንዲዳብር የፖለቲካ ፓርቲዎች ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ኦህዴድ በሚገባ ይገነዘባል፡፡ የሀገራችን ሕዝቦች አማራጭ ሀሳቦች እየቀረቡለት በዴሞክራሲያዊ ሂደት የሚጠቅመውን ሃሳብ እንዲመርጥ፣ለፖለቲካ ፓርቲዎች በሕገመንግስቱ የተቀመጡ ቃልኪዳኖች ያለመሸራረፍ እንዲተገበሩና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ኦህዴድ ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፖርቲዎች ጋር በቅርበት እንደሚሰራ በጥልቅ ተወያይቶበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ በዚሁ መሰረት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያላችሁ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ልዩነታችን እንደተጠበቀ ሆኖ በሀገራችንና በሕዝባችን የጋራ ጥቅምላይ ከድርጅታችን ኦህዴድ ጋር አብራችሁን እንድትሰሩ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች
================================
የኢትዮጵያ ብሔር፤ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በችግርም ሆነ በመልካም ጊዜ በጋራ ተፈትነው ትላንትን መሻገር ችለዋል፡፡ ለገጠማቸው ፈተናዎችምእኩል የታገሉና መሰዋትነት የከፈሉ ህዝቦች ናቸው፡፡ ሀገራችን ህልዉ ሆና እድትቀጥል ከማስቻላቸዉ ባሻገር በዓለም ታሪክ ውስጥ ጉልህ ቀለም እንዲኖራት አድርገውለዛሬ ትውልድ አሰረክበዋል፡፡በአባቶቻችን ተጋድሎ የተገነባችውን ኢትዮጵያ እኛም አስውበንና አንድነቷን አስጠብቀን ለቀጣይ ትዉልድ የማሻገር ታርካዊ ኃላፍነት አለብን፡፡በአንድ እጅ ማጨብጨብ አይቻልምና ይህን ሀላፍነታችን በብቃት እንድንወጣ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትንበማጠናከር፣ የጋራ እሴቶቻችንን በማጎልበት፣ የተጀመረው መልካም ጅማሮ ዳር እንዲደርስ እጅ ለእጅ ተያይዘን ለስኬቱ በጋራ እንድንረባረብ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴየ10 ቀናት የለዉጥ ግምገማ ቆይታ ድርጅቱ ለሃገራችን ሰለም ልማትና ዴሞክራሲ ጉዞ ስኬት እንዲሁም ለህዝቦች እኩል ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ከመቼዉም ግዜ በላይ በላቀ ቁርጠኝንትና ተነሳሽነት ለማከናዉን ዝግጁነቱን ያረጋገጠበት መድረክ እነደሆነ የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አረጋግጦዋል
የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ
ጥር 29/05/2010 ዓ.ም

Image may contain: 1 person, suit


Thursday, December 28, 2017

በጦርነት እየታመሰች ባለችው የመን ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የሚደርስልን አጣን እያሉ ነው።

በቅርቡ በነበረው ጦርነት በሰንዓ ከተማ ሁለት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጥይት ተመተው እግራቸው ተቆርጧል
በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት የሚደርስልን አጥተን ለእንግልት ተዳርገናል ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
እነዚህ ስደተኞች አብዛኞቹ ሰንዓ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ቢሆንም አሁን ግን በጦርነቱ ምክንያት ወደ ተለያዩ የገጠር አካባቢዎች እየተሰደዱ እንደሆነ እና መፍትሄም እንዳጡ ይናገራሉ።
ጀማል ጄይላን ከ16 ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ወጥቶ በየመን መኖር የጀመረ ሲሆን "ሀገሪቱ በጦርነት እየታመሰች ስለሆነ የሚደርስልን አጥተናል" ይላል።
"ስለዚህ ችግራችንን የምንነግረው አንድም አካል የለም፤ ስንታመም የምንታከምበት ቦታ የለም፤ ብዙ ልጆች ያሏቸው ሰዎች አሉ። ከፍተኛ እንግልት እየደረሰብን ነው" በማለት ያሉበትን ሁኔታ አስረድቷል።
ከዚህ በተጨማሪ "በጦርነቱ ምክንያት ሥራ የለም። ለሰራንበትም ደሞዝ አይከፈለንም፤ ቢከፈለንም ዝቅተኛ ነው። የምግብ ዋጋ ደግሞ እጅጉን ንሯል" ሲል ሁኔታቸውን ይገልፃል።
ሌላኛው ለ17 ዓመት የመን ውስጥ የኖረው ኤርትራዊ እና ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀን ግለሰብ ደግሞ በየመን መንግሥት እና በአማፅያን መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ስደተኞች እየተጎዱ መሆኑን ተናግሯል።
"ሀገሪቱ በጦርነቱ ምክንያት አዲስ ስደተኛ መመዝገብ ካቆመችም ሁለት ዓመት ሆኗታል።"
ስለዚህ ወደ የመን የሚሄዱ ስደተኞች መታወቂያ ከማጣታቸውም በላይ ቀድመው እንኳ መታወቂያውን ያገኙ ማሳደስ አለመቻላቸውን ይናገራል።
አማፅያኑ መግቢያና መውጫ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን ጦርነቱን በመሸሽ ለማምለጥ የሚሞክሩ ስደተኞች ለወታደሮች ጥቃት እየተጋለጡ እንደሆነም ይገልፃል።
በቅርቡ በነበረው ጦርነት እንኳ በሰንዓ ከተማ ጎዳናዎች ሁለት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጥይት ተመተው በደረሰባቸው ጉዳት እግራቸው ተቆርጦ አሁን ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ እንደሆነ ጀማል ይናገራል።
መንገድ ላይ መዘረፍ፣ መታሰር፣ ገንዘብ ከቤተሰብ እንድናስልክ መገደድ እና የመሳሰሉትን ቀድሞም ቢሆን ለምደነዋል፤ የሚለው ኤርትራዊው ስደተኛ በሀገሪቱ ያለው ጦርነት ከመባባሱ ጋር ተያይዞ ግን አንዳንዶች ተገደው ወደ ውትድርና እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ተናግሯል።
ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ማለዳ ላይ በዘጠኝ የሁቲ ፖሊሶች ተደብድቤያለሁ፤ የሚለው አማን መሀመድ መታወቂያውን ቤት ውስጥ ረስቶ መውጣቱን ቢናገርም እንኳ ከከተማዋ ወጣ ባለች የገጠር አካባቢ ወስደው እንደደበደቡት ይናገራል። ከድብደባው በተጨማሪም 330ሺህ የየመን ሪያል መዘረፉንም ይገልፃል።
"ለአንድ ሰው 9 ወታደር ማለት ከባድ ነው። እንደ እባብ ነው የቀጠቀጡኝ። ራሴን እንድስት ከመኪና ጋር አጋጩኝ። ከዚያም ወደ ጦር ሜዳ ሊወስዱኝ ነበር። በኋላም ሁቲዎችን በሚቃወም አንድ ወታደር ነው ነፍሴ ለመትረፍ የቻለው" ይላል አማን።
ኢትዮጵያዊያን፣ ኤርትራዊያን እና ሶማሌያዊያን የስደተኞች ማህበረሰብ አባላት በጋራ በመሆን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የየመኑን ቅርንጫፍ ሄደው ድጋፍ እንዲደረግላቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ይናገራሉ።
የመንImage copyrightMOHAMMED HUWAIS
አጭር የምስል መግለጫየመን ሰነዓ
የቀድሞው ፕሬዝዳንት አሊ አብዱላህ ሳላህ በተገደሉበት ወቅት በሀገሪቱ ያለው ውጥረት ተባብሶ እንደነበር የሚናገሩት እነዚህ ስደተኞች፤ በዚህም ምክንያት የከፋ ችግር ገጥሟቸዋል።
እየደረሰባቸው ያለውንም ችግር ጠቅሰው ኮሚሽኑን እርዳታ ቢጠይቁም አልተዘጋጀንበትም የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው እና በድጋሚ ጥያቄውን አቅርበው ምንም የምናግዛችሁ ነገር የለም የአካል ጉዳት ያለበት ስደተኛ ካልሆነ በቀር በጀት የለንም መባላቸውን ገልፀዋል።
የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ድርጅትም ''የእኛ ድርሻ ጦርነት በተነሳ ወቅት ከጦርነቱ ቀጠና መውጣት ያልቻሉ ሰዎችን ወደ ሰላማዊ ስፍራ መውሰድ ነው'' ማለቱን እነዚሁ ስደተኞች ተናግረዋል።
ስደተኞቹ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የሚገኙበትን ሁኔታ ለዓለም እንዲያሳውቅ ካልሆነ ደግሞ ከየመን መውጣት የሚችሉበትን ሁኔታ እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
የአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ቃል አቀባይ ሊዮናርዶ ዶይል፤ ቀድሞም ቢሆን ፍልሰት መኖሩን ጠቅሰው ከአፍሪካ ቀንድ የሚሰደዱ ግለሰቦች ቀውስ ውስጥ በምትገኝ ሀገር ውስጥ በጦርነት መሃል ይገኛሉ ብለዋል።
"ሰዎችን አትሰደዱ አንልም ነገር ግን በተቻለ መጠን ከወንጀለኛ እና ደላሎች ራሳቸውን ጠብቀው ደህንነቱ የተጠበቀ ስደት እንዲያደርጉ እንፈልጋለን"ብለዋል። Read more here

Tuesday, December 26, 2017

መረጋጋት ያልቻሉት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

ትምህርት ሚኒስቴር
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተማሪዎች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶች የትምህርት መቋረጥን በተደጋጋሚ ከማስከተላቸው በተጨማሪ ተማሪዎች ተረጋግተው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ሥጋት ፈጥረዋል።
በተለይም በተማሪዎች መካከል ማንነትን መሰረት አድርገው የሚነሱ ግጭቶችን ተከትሎ በተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። የአካል ጉዳት ከመድረሱም በተጨማሪ ንብረትም ወድሟል።
ይህ ክስተትም የመማር ማስተማር ሂደቱን ከማስተጓጎሉም ባሻገር ጥቂት የማይባሉ ተማሪዎች ለደህንነታቸው በመስጋት ወደየመጡበት ለመመለስ ሲገደዱ፤ ሌሎች ደግሞ ስጋት ዉስጥ ሆነው በየዩኒቨርሲቲዎቹ ባለተረጋጋ መንፈስ ይገኛሉ።
መንግሥት ነገሩን ለማረጋጋት በትምህርት ተቋማቱ ውስጥ የፀጥታ ኃይሎችን ከማሰማራቱ በተጨማሪ በዩኒቨርሲቲዎቹ የሰዓት እላፊ ገደብ ለመጣልም ተገዷል።
በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲ ኃላፊዎች ከመንግሥት ተጠሪዎች ጋር በመሆን ከተማሪዎች ጋር ውይይት እያደረጉ መሆናቸዉንና የተማሪዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊውን ነገር እያደረጉ መሆኑን ቢገልፁም ተማሪዎች፣ መምህራንምና ወላጆች አሁንም ስጋታቸው አልተቀረፈም።
"ሰግተናል"
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የነበሩ በርካታ ተማሪዎች በየተቋሞቻቸው ባጋጠሙ ግጭቶች ሳቢያ ለደህንነታቸው በመስጋት የጀመሩትን ትምህርት አቋርጠው ወደየመጡበት አካባቢ ለመመለስ እንደተገደዱ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ባለፉት ሳምንታት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸዉ ሲከታተሉ የነበሩ በርካታ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ማደሪያ አጥተዉ ሲንገላቱ ቆይተው ብዙዎቹ ወደ ትዉልድ ቦታቸዉ መመለሳቸውን አብረዋቸው የነበሩ ተማሪዎች ተናግረዋል።
እነዚህን ተማሪዎች የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጉዳዮች ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ያናገሯቸዉ ቢሆንም ተገቢውን ምላሽ እንዳላገኙ ተማሪዎቹ ይናገራሉ።
ከተማሪዎቹ መካከልም አንዱ "አሁን ባለዉ ሁኔታ ወደመጣንበት ዩኒቨርሲቲ ተመልሰን መሄድ ስለማንችል፤ በአካባቢያችን ወደ ሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲመድቡን ጠይቀን ነበር። ትምህርት ሚኒስቴር ግን አግባብ ያለው ምላሽ አልሰጠንም" ብሏል።
"የዓመቱ ትምህርት ሲጀመር አንስቶ የተረጋጋ ሁኔታ አልነበረም" የሚለውና ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገው የወለጋ ዩኒቨርሲቲ የምህንድስና ተማሪው ''ሁሌ አንድ የሚረብሽ ነገር አይታጣም። ወደ ግጭት ደረጃ ሲደርስ ደግሞ እራሴን ማትረፍ ስለነበረብኝ ከግቢ ወጥቻለዉ" ሲል ይናገራል።
የተለያዩ ተማሪዎች እንደሚሉት በዩኒቨሲቲዎቹ የሚነሱት ግጭቶችና ጥቃቶች በቀላል አጋጣሚ የሚጀመሩ ቢሆንም እንኳን የሚያስከትሉት ጉዳት ቀላል የሚባል አይደለም። የሚደርሰውን ጉዳትም ለመከላከል ተቀናጅቶ በአንድነት የሚሰራ አካል ባለመኖሩ የከፋ ሁኔታ እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑንም ይጠቅሳሉ።
እንዴት ተጀመረ?
በምንማርባቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሚከሰቱ ግጭቶችና ጥቃቶች ሳቢያ ደህንነት ተሰምቶን ትምህርታችንን መከታተል አልቻልንም ያሉ ተማሪዎች በሩን ያንኳኩበት የትምህርት ሚኒስቴር፤ ችግሩ የሃገሪቷን ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎች የፈጠሩት እንጂ የህዝቡም ሆነ የተማሪዎቹ ችግር አይደለም ብሎ ያምናል።
ነገር ግን ባጋጠሙት ነገሮች ምክንያት ተማሪዎቹን በየክልላቸዉ መመደብ ግን እንደማይቻል፤ ዩኒቨርሲቲዎችም የፌደራል መንግሥት ተቋማት እንጂ የክልሎች አይደሉም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
በሁሉም የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች፤ ጥያቄያቸዉን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማቅረብ ይገባቸዋል የሚሉት የትምህርት ሚኒስቴር የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ ሃረጓ ማሞ፤ አሁን ያለውን ችግር ለመፍታት ጉዳዩን በተለይ የሚከታተል ክፍል እንደተደራጀ ገልጸዋል።
ከዚህ ባለፈ ግን ችግሩ የአስተሳሰብ ክፍተት የፈጠረዉ በመሆኑ በቀጣይ ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ይናገራሉ።
ይሁን እንጂ የተማሪዎቹ ስሜት ከዚህ የተለየ ነዉ። መንግሥት የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ስለሚሰራቸዉ ሥራዎች እርግጠኞች ስላልሆኑ አሁንም ስጋታቸውን የሚቀርፍ እርምጃ አላየንም ባይ ናቸዉ።
ከዚህ በተቃራኒ ሌሎች ደግሞ በየዩኒቨርስቲዎች የተፈጠሩ ግጭቶችን ለማብረድና ለማረጋጋት የተሰማሩ የፀጥታ ኃይሎች ስጋት እንደሆኑባቸው የሚናገሩ ተማሪዎችም አሉ።
ካለመረጋጋቱ በኋላ ወደሚማርበት የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተመለሰው ሌላኛው ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ተማሪ እንደሚለው እርሱና ጓደኞቹ ወደ ትምህርታቸው የተመለሱት ጥያቄያቸው ተመልሶ ሳይሆን በሁኔታዎች ተገደን ነው ይላል።
ተማሪዎቹ አሁንም ቢሆን በግቢው የጦር መሳሪያ የያዙ ሃይሎች መገኘት ፍርሃት እንደፈጠረባቸው ይናገራሉ።
ከሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ያናገርናቸው ተማሪዎችም ግቢዉ በጸጥታ ኃይሎች መወረሩን ይናገራሉ።
ወደ ትምህርት የተመለሱ ቢሆንም ያለው ሁኔታ መረጋጋትን የሚያመለክት ስላልሆነ ትምህርታቸው ላይ ማተኮር በሚችሉበት የሥነ-ልቦና ሁኔታ ላይ አለመሆናቸውን የገለፁ ተማሪዎችም አሉ።
የትምህርት ሚኒስቴር አርማImage copyrightMMINISTRY OF EDUCATION
የወላጆች ጭንቀት
ልጆቻቸውን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለይም ግጭቶች ወደ ጎሉባቸው የላኩ ቤተሰቦች ከባድ ችግር ውስጥ እንደሚሆኑ አያጠራጥርም። የልጆቻቸው በተቋማቱ መገኘት ለደህንነታቸው እንዲሰጉ ያደርጋቸዋል።
በሌላ በኩል ልጆቻቸውን ከቤት እንዲቀሩ ማድረግ ደግሞ በቀጣይ ትምህርታቸው እንዴት ይሆናል በማለት ያስጨንቃቸዋል።
ሴት ልጃቸውን ከአዲስ አበባ ባለፈው ዓመት ወደ ዩኒቨርሰቲ የላኩት አቶ መኮንን በየጊዜው በፍርሃት የተዋጠ ድምጿንና የብሄር ግጭቶችን ወሬ መስማት ጭንቀት ውስጥ እንደከተታቸው ይናገራሉ።
"አምኜ የላኳት አንድ ፍሬ ልጄ መማሩ ቀርቶ በሰላም ስለመኖር ስትጨነቅ ስሰማ በጣም ያሳዝነኛል፤ ሁሉ ቀርቶብኝ እንድትመለስልኝ ብፈልግም መግባት መውጣት አይቻልም ብላኝ ይኸው በጭንቀት ውስጥ ነኝ" ይላሉ።
ልጆቻቸው ያሉበትን ሁኔታ በትክክል የሚያስረዳና መረጃ የሚሰጥ አካል አለመኖሩ ደግሞ ስጋታቸውን እንደጨመረው ይናገራሉ አቶ መኮንን።
"ምነው እንደምንም ተቸግሬ እዚሁ ባስተምራትስ? በምን ክፉ ቀን ነው የላኳት እያልኩ እጸጸታለሁ፤ ብቻ ይሄ ቀን አልፎ በሰላም ትመለስልኝ እንጂ ዋስትና ሳላገኝ ልጄን አልካትም።''
ልጃቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ትምህርት ቤት እያስተማሩ ያሉ ሌላኛው አባትም ነገሩ ለወላጆች እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ይናገራሉ።
የእርሳቸው ልጅ በሚማርበት የትምህርት ተቋም እስካሁን ምንም ዓይነት ግጭት ባለመፈጠሩ ልጃቸው ትምህርቱን እየተከታተለ ቢሆንም፤ የቅርብ ዘመዶችና ጎረቤቶቻቸው ልጆቻቸውን በተለያዩ ክልሎች ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እያስመጡ እንደሆነ ይናገራሉ።
"የማውቃቸው ወላጆች ከተለያዩ ክልሎች ልጆቻቸውን እያስመጡ ነው። የእኔ ልጅ ባለበት ነገሮች ደህና ቢሆኑም የሌሎች ወላጆች ችግር በጣም ይሰማኛል "ይላሉ።
ባለፍው ዓመት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የነበረውን አለመረጋጋት በማሰብ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ ጨርሶ ልጆቻቸውን ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲዎች ያልላኩ ቤተሰቦችንም ያውቃሉ።
እነዚህ ቤተሰቦች ልጆቻቸውን አዲስ አባባ ውስጥ በተለያዩ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለማስተማር የወሰኑ ናቸው።
ነገሮች ተስተካክለው ዩኒቨርሲቲዎችም ወደ መደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት እንዲመለሱም "በዩኒቨርሲቲዎች የሚታየው ነገር በማህበረሰቡ ያለው ፖለቲካ ትኩሳት ነፀብራቅ ነው። ስለዚህ በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን ነገር ለመፍታት መጀመሪያ የህዝቡ ጥያቄ ምላሽ ማግኘት አለበት" በማለት እኚህ አባት ሃሳባቸውን ይሰነዝራሉ።
''በዚህ ወቅት በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ስለሚከሰቱ ነገሮች እርግጠኛ መሆን አይቻልም። ዛሬ ሰላም ቢሆን ነገ ሌላ ይሆናል። ለዚህም ነው ከእኔ ርቆ የሚገኘው ልጄ ደህንነት ዘወትር የሚያሳስበኝ። መረጋጋት አልቻልኩም'' ይላሉ ሌላ ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ እናት።
ላለፉት ሳምንታት ካለበት ዩኒቨርሲቲ ተመልሶ ነገሮች እስኪረጋጉ ልጃቸው ከእርሳቸው ጋር እንዲቆይ እንዳደረጉ የሚናገሩት እናት በየዕለቱ የልጃቸውን ውሎ ይከታተላሉ። ''ምንም እንኳን ያለበት ቦታ እሩቅ ቢሆንም ዘወትር እደውልለታለሁ፤ ስልክ አልሰራ ሲለኝ በጣም እጨነቃለሁ''ይላሉ።
እኚህ እናት ስለልጃቸው ደህንነት መጨነቃቸው የሚያበቃበትን ጊዜ ይናፍቃሉ፤ ''መንግሥት ሕዝቡ የሚለውን መስማት አለበት። ካልሆነ ግን ነገሮች ከቁጥጥር እየወጡ ነው። ወደከፋ አቅጣጫ እያመራን እንደሆነ መገመት አይከብድም'' በማለት ያክላሉ።
የባህር ዳር ነዋሪ የሆኑትና ልጃቸው የሁለተኛ ዓመት የኢኮኖሚክስ ተማሪ እንደሆነች የሚናገሩት አቶ ይላቅም መፍትሄው በመንግሥት እጅ መሆኑን ጠቅሰው፤ እርሳቸውም የልጃቸው ደህንነት እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል።
''ይህ አሁን የምናየው ችግር ፖለቲካው ለዓመታት ሃገሪቱን የወሰደበት መንገድ ውጤት በመሆኑ አዝናለሁ። በቀደመው ዘመን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለጭቁኑ ሲጮሁና ሲንገላቱ ነበር የምናውቀው፤ አሁን ግን እርስ በርስ የጎሪጥ መተያየታቸው የተጓዝንበት መንገድን አደገኝነት የሚያሳይ ነው'' በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።
ልጃቸው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ህክምና እያጠና ያለው አባትም የአቶ ይላቅን ሃሳብ ይጋራሉ። በዩኒቨርሲቲዎች ዛሬ እየታየ ያለው ነገር ኢህአዴግ ላለፉት ዓመታት ያራመደው ፖለቲካ ውጤት እንደሆነ ያስረዳሉ።
ተኽላይ ገብረንስአ የተሰኘው ወላጅ ከስድስተኛ ክፍል ጀምሮ ከገጠር አምጥቶ ያስተማረው ወንድሙ ይማርበት ከነበረው ዩኒቨርስቲ ትምህርቱን ኣቋርጦ እንዲመለስ አድርጓል። ትምህርቱ ቢቋረጥም ወንድሙ በህይወት በመመለሱ ብቻ ደስተኛ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግሯል።
"ጎበዝ ተማሪ ስለነበር ትምህርቱን ጨርሶ ታናናሾቹን ይጠቅማል የሚል እምነት ነበረኝ። ይሁን እንጂ አሁን ወንድሜ ሥነ-ልቦናው እጅግ ተጎድቷል። ከመጣ ጀምሮም ከቤት አይወጣም። ነገሩ ለታናሽ ወንደሞቹም ተስፋ አስቆራጭ ነው" ይላል።
ትምህርት ጥያቄ ውስጥ ሲወድቅ
እየተስተዋሉ ባሉት ክስተቶች ተጨንቀው የሚገኙት ተማሪዎችና ወላጆች ብቻ ሳይሆኑ ሁኔታው በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚያስተምሩ መምህራንም ስጋት አላቸው።
ስማቸውና የሚያስተምሩበት ተቋም እንዳይጠቀስ የጠየቁት መምህር እንደሚሉት አሁን እየታዩ ያሉት ግጭቶችና ጥቃቶች ድንገት የተከሰቱ ነገሮች አይደሉም።
''ትምህርት ከፖለቲካ ሥርዓቱ ጋር ተጣብቆ ከታችኛው የትምህርት ደረጃ ጀምሮ ለዓመታት ሲዘራ የነበረው የጥላቻ ፖለቲካ ውጤት ነው'' ይላሉ።
ይህ ደግሞ በተለያዩ አጋጣሚዎች በክፍል ውስጥ ሲያጋጥም እንደታዘቡ የሚናገሩት መምህር ''አሁን ገንፍሎ ይፋ የወጣው ሃገሪቱ ውስጥ ያለውን ፖለቲካዊ ውጥረት ተከትሎ ነው።''
በአዲስ አበባ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ እስራኤል ተሰማ ደግሞ ክስተቶቹ በትምህርት ሂደቱ ላይ ከባድ ተፅዕኖ እንደሚያሳድሩ ይናገራሉ።
በተማሪዎች ላይ የሚፈጠረው ስጋት የትምህርት ፍላጎታቸውንና ዝግጁነታቸውን ይቀንሰዋል። ትምህርት የተቋረጠባቸውን ጊዜያት ለማካካስ የሚደረገው ጥረትም በተማሪዎችና በመምህራን ውጤታማነት ላይ ተፅዕኖ አለው ይላሉ።
አቶ እስራኤል ''እንዲህ አይነት የእቅድ መዛባቶች በትምህርት ተቋማቱ ፕሮግራም ላይ መስተጓጎልን ከማስከተል በተጨማሪ በትምህርት ጥራት ላይ ችግር ያስከትላሉ'' ይላሉ።
ነገሮች ተረጋግተው ተማሪዎችም ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እየተመለሱ እንደሆነ ሲገለፅ የነበረ ቢሆንም የተለያዩ የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ከቀናት በፊት በመቱ እንዲሁም በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት መቋረጡን ዘግበዋል። Read more here
Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time