Sunday, May 13, 2018

የአማራ ብሔርተኝነት ወግ በቤተ መንግሥት

የአማራ ብሔርተኝነት ወግ በቤተ መንግሥት

በአማራ ክልል ከሚገኙ ዞኖች የተጠሩ በርካታ ሰዎች ታድመዋል፡፡ ከአዲስ አበባም በጣት የሚቆጠሩ አማራዎችም ተገኝተዋል፡፡ አመሻሹ 11፡30 ላይ ከታችኛው ቤተ መንግሥት (ኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት) ተገኘን፡፡ 12፡00 ገደማ ላይ በቤተ መንግሥቱ የእንግዳ መቀበያ የተለያዩ መጠጦች ለሚፈልግ ሰው ይሰጡ ነበር፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ጃንሆይ (ዐጼ ኃይለ ሥላሴ) ግብር ከሚያበሉበት አዳራሽ ገብተን ታደምን፡፡
በጣት ከሚቆጠሩ ደቂቃዎች በኋላ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ (ዶ/ር አቢይ አህመድ)፣ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ (አቶ ደመቀ መኮንን)፣የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ( አቶ ብናልፍ አንዷለም)፣የክልሉ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ወደ መድረኩ መጡ፡፡
በመቀጠል አቶ ንግሡ ስለፕሮግራሙ በማስተዋወቅ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ የምግቢያ ንግግር እንዲያደርጉ ጋበዟቸው፡፡
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የመግቢያ ንግግር በአጭሩ፤

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ አንድነት፣ ስለ ፍቅር፣ይቅር ስለመባባል ጠቀሜታና ፋይዳ ሰፋ ያለ ንግግር አደረጉ፡፡ በተለይ ስለይቅርታ ሁለት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ አንደኛው የደርግ ባለሥልጣናትን የሚመለከት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በውጭ አገር የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ነው፡፡
እንደ እሳቸው ገለጻ ወደ 23, 000 የሚደርስ ቁጥር ከቀይ ሽብር እና ደርግ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያን ጥሎ የተሰደደ ወይም በውጭ አገር የሚኖር ኢትዮጵያ አለ፡፡ ይቅር ተባብለን አገራቸው ገብተው በሰላም መኖር አለባቸው አሉ፡፡ የቀድሞው ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያምንም ይቀርታ አድርገንላቸው አገራቸው መጥተው መኖር አለባቸው አሉ፡፡
ስለ ሲኖዶሱ ሲናገሩም ፓትርያኩን አቡነ ማትያስን እንዳገኟቸውና ውጭ ስላለው ሲደኖዶስ እንዳወያይዋቸው፤ ሰላም ወርዶ አንድ ሆነው ጠንካራ ቤተ ክርስቲያን እንድትኖር ምኞታቸው እንደሆነ እንደገለጹላቸው ተናግረዋል፡፡
በመቀጠል በተለይ የብሔርተኝነትን ነገር ሲያነሱ ባልተቤታቸውን (ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽን) ምሳሌ በማድረግ ጉዳዩን ማብራራት ቀጠሉ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ በዚህ የእራት ግብዣ ላይ ቀዳማዊት እመቤቷ ታድመዋል፡፡ ሌሎች ግብዣዎች ላይ እንዳልተገኙ ገልጸው የዕለቱ ግብዣ ግን የአማራዎች እንደሆነ ሲነገራቸው እንደመጡ ተናገሩ፡፡ ይህንን ሲናገሩ እኛ አጨበጨብን፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን የሚያስጨበጭብ አይደለም አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለፍቅር፣ስለአንድነት፣ስለይቅርባይነት በርካታ ቁምነገሮችን አካፈሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረው እንደጨረሱ አቶ ንጉሡ መድሩኩን እንዲመሩ ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ጋበዙ፡፡ ዳንኤልም መጠነኛ ንግግር አድረጎ ውይይቱን በመምራት ለተለያዩ ሰዎች ዕድል ሠጡ፡፡
የእለቱ ሁለት ዓይነት ታዳሚዎች፤
=============
ታዳሚ አንድ-ኢትዮጵያዊያኖቹ ብቻ
---------------
ያው እንደተለመደው በርካታ አባቶቻቸችን እና እናቶቻችን አማራ የሚታወቅበትን የኢትዮጵያዊነት ባህርይ አስተጋብተዋል፡፡ አንዳንድ ወጣቶችም በተመሳሳይ በዚሁ መንገድ ተጉዘዋል፡፡ ስለ ልማትና ተያያዥ ጉዳዮች አንስተዋል፡፡
ታዳሚ ሁለት-አማራየሆኑ ኢትዮጵያዊያኖቹ፤
---------------------------
በዚህ ምድብ ሥር የሚካተቱት ስለአማራ ብሔርተኝነት መንስኤውም ግቡም ከኢትዮጵያዊነት ጋር ስላለው ግንኙነትም አብራርተዋል፡፡ አስረድተዋል፡፡ የአማራ ብሔርተኝነት የተወለደው በበደል፣በመከፋት፣በመገፋት ነው፡፡ እንኳንስ ለኢትዮጵያ ለመላው ጥቁር ሕዝብ መኩሪያ በሆነው ታሪኩ እንዲያፍርበት ተሠራ፡፡ እምዬ ምኒልክን ያህል መሪ ስም መጥራት እንኳን እንዲያሸማቅቅ ተደረገ፡፡ አማራ አገር ቢያቀና ነፍጠኛ ተባለ፡፡ ኢትዮጵያዊ ነኝ ሲል ማን ኢትዮጵያዊ ያልሆነ አለ ተብሎ ትምክህተኛ ተባለ፡፡ በተለይ በሁለተኛው ሚኒሊየም (ከ1000-2000 ) በተካነወኑ የአማራ ታሪኮች አማራ እንዲያፍር ሌት ተቀን ተሠራ፡፡ ቀና እንዳይል በሚያሸቅቅ ሁኔታ ደባ እና በደል እተሠራበት፡፡ በመሆኑም ከታሪኩም ከባህሉም እንዲነጠል በተደራጀ መንገድ ተዘመተበት፡፡
ከኢኮኖሚውም እንዴት እንደተነጠ እና እንደተበደለ በርካታ ማነጻጸሪዎች እየቀረቡ አስተያየት ተሠጠ፡፡ ለአብነትም በኢትዮጵያ ካሉ ደረጃ አንድ ኮንትራክተሮች ውስጥ እንደው ስም ያለው አንድ ኮንትራክተር አለን? የሚል ጥያቄያዊ ትችት ቀረበ፡፡ ከኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካውም የደረሰበበትን መገለል ተነግሯል፡፡ በመሆኑም የአማራ ብሔርተኝነትን የፈጠረው ከ1983 ዓ.ም. በኋላ የደረሰበት በደል እንደሆነ በበርካታ ወንድምና እህቶች ተብራርቷል፡፡ (የአንዳንዶቹን ስም ያልገለጽኩት ያው በሚታወቅ ምክንያት ነው፡፡ )
የአማራ ብሔርተኝነት ለማንም ስጋት እንደማይሆን በተለይ ዶ/ር ሲሳይ መንግሥቴ አብራርተዋል፡፡ ሕወሃት ስትመሠረት ጠላት አብጅታ ነው፡፡ አማራን ጠላት አድረጋ፡፡ የአማራ ብሔርተኝነት ግን ማንንም በጠላትነት አልሳለም፡፡ ራሱን ለመከላከል እንጂ፡፡ (ነገሩ ያው የመክት ጉዳይ ነው!) አማራ መቼም ቢሆን መቼም በኢትዮጵያዊነት አይደራደርም፡፡ ነገር ግን አማራ ደግሞ ላይመለስ አማራ ሆኗል፤ አማራ ነው፡፡ በመሆኑም የአማራ ብሔርተኝነት ለማንም ስጋት እንዳልሆነ ተብራርቷል፡፡
አብሮ በመድረኩ የተነሳው አማራ ክልልም ሆነ ብአዴን፣ ጸረ አማራ ወይም አማራ ጠል ከሆኑ አማራሮች እንዲላቀቅ ነው፡፡ እነዚህ አማራን የሚጠሉ ጸረ አማራ አመራሮች አማራን በመምራትም ሆነ እንደ ጆፌ አሞራ ሌሎችን በመዞርና አማራን በማጥቃት መቀጠል እንደሌለባቸውም ተወስቷል፡፡
በተለይ ከየክልሉ የሚፈናቀሉ አማራዎች ጉዳይ በዚህ ምሽትም ትኩረት ተሰጥቶበታል፡፡ ብጹእ አባታችን አቡነ አብርሃም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
የወሎ ቴሪሸሪኬር ሆስፒታልም ብዙ ሰው ከተናገረበት ጉዳይ አንዱ ነበር፡፡ ከከሚሴና አካባቢዋ የታደሙት አባቶች በአሸባሪነት ተከሰው ስለደረሰባቸው ግፍ ( ሽንት ሁሉ ይሸናባቸው እንደነበር) ሁሉንም ሰው ወደ ሐዘን ድባብ በከተተ ሁኔታ ተናግረዋል፡፡ ከሰሜን ወሎ የመጡ አንድ ጎልማሳም ስለወልዲያ፣ቆቦና መርሳ ሁኔታ ተናግረዋል፡፡ ሼክ አሊ አላሙዲንንም ለማስፈታት እንዲሞክሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዝጊያ ንግግራቸው፤
===============
በታወቀው ንግግር አዋቂነታቸው እና በበርካታ ምሳሌዎች አሁንም ስለመተባበር፣ስለ አንድነት፣ ስለ ይቅር ባይነት በተለይም እምዬ ምኒልክን በምሳሌነት በማንሳት አስረድተዋል፡፡ የንጉሥ ተክለሃይማኖትና የእምዬን ታሪክ አውስተዋል፡፡ ማርከው የሚያክሙ እንዲሁም የሚሾሙ መሆናቸውን እና ይቅር ባይነታቸውን በአርያነት አንስተው አስረድተዋል፡፡
በመጋረጃ የተሸፋፈነውን የጃንሆይን ዙፋን አስከፍተው መኩሪያችን እንደሆነ፣ከመስከረም ጀምሮ ለሕዝብ ክፍት እንደሚሆን ሁሉ ተናገሩ፡፡ ላይኛው ቤተ መንግሥትንም (የምኒሊክ ቤተ መንግሥትንም)አስደናቂነት እና ሁላችንም የየድርሻችንን መወጣት እንዳለብን ተናግረዋል፡፡
የወሎ ቴሪሸሪ ኬር ሆስፒታልንም ከአቶ ደመቀ ጋር እንደተነጋገሩ እና ትኩረት እንደሚሰጡበት ተናግረዋል፡፡
የሼክ አሊ አላሙዲን ጉዳይንና ሌሎች በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ እሰረኞችን በሚመለከት ለመወያየት የፊተችን ሐሙስ ወደ ሳዑዲ እንደሚሔዱ ነግረውናል፡፡
ሦስት የመውጪያ ወጎች፤
========
አንድ
-----
አንዳንድ ሰዎች፣በዚሁ መድረክም ጭምር፣ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ ቦታዎች መዟዟር እና መንቀሳቀስ ስላበዙ ጊዜ እንስጣቸው፤አሁን በየቦታው ቢዞሩም ቢሮ ሆነው ሥራ ባይሰሩም የሚል አንድምታ ያለው ንግግር ስለበዛ ይመስላል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መደበኛ ሥራቸውን እና ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮችን እንደውም ከወትሮው በበለጠ ሁኔታ እየሠሩ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ሁለት፤
------
ጠቅላዩ በዚሁ ግብር ላይም ጭምር እንደታየው ስለደረሰ በደል ስለተወራ እሳቸውም ብዙዎቻችን ተበድለናል አሉ፡፡ ለዚህም ደግሞ ፊታቸው ላይ የወጣውን ማድያት አሳዩን፡፡ ስለማዲያቱ ሁኔታ ይምታውቀው ባልተቤታቸው እንደሆነችም ተናገሩ፡፡
( ይቺን ነገር ለታዳሚው ከመናገራቸው በፊት በእራት ሰዓት እኔና ጓደኞቼ (ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣አንዷለም አባተ/የአጸዴ ልጅ፣ምንዳራለው ዘውዴ፣ዶ/ር ሰጥአርጋቸው) ወደተቀመጥንበት መጥው ስለነበር የእኔን እጅ ይዝው ፊታቸውን አሳዩኝ፡፡) ፊቴን ማድያት በማዲያት እንዲሆን ያደረጉትን ልበቀል ብል ስንት ሰው ማሰር አለብኝ? አሉ፡፡ በመበቃቀል ፍቅር አይገነባም አሉ፡፡
ሦስት፤
------
የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር የአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ስም በብዙ ሰዎች በበጎ ተነስቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም እንዲህ አሉ፡፡ ሰዎች ብዙ ጊዜ በአድናቆት የሚናገሩት ስለ አቶ ገዱና አቶ ለማ መገርሳ እንዲሁም አልፎ አልፎ ስለ እኔ ነው አሉ፡፡ ነገር ግን መርሳት የሌለባችሁ ከእኛ ጀርባ አንድ ሰው ያሉ መሆናቸውን ነው አሉ፡፡ እሳቸውም አቶ ደመቀ መኮንን ናቸው አሉ፡፡
በሉ ደህና እደሩ፡፡ ከምሽቱ 4፡30 አካባቢ ውይይቱ ተጠናቀቀ፡፡ እኔም ሌሊት ጻፍኩት፡፡ ለቴሌቪዥንም ይሁን ለሬዲዮ ቀረጻ አልተደረገም፡፡ ሞባይልም ካሜራም የለም፡፡"
(ውብሸት ሙላት)

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ ሃገራት ሰዎች...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል በዚህ ሳምንት ከ27 በላይ የሚሆኑ ‘ሰላማዊ ሰዎች’ “በመንግሥት ኃይሎች” መገደላቸው ተነገረ
     በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “የመንግሥት ኃይሎች” ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።የደብረሲና ከተማጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19፤ 2016 ዓ/ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን፤ በጥቃቶቹም ከ27 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር...
    June-29 - 2024 | More »
  • AMHARA MASSACRE: A GRIM REMINDER OF ETHIOPIA’S FRAGILE PEACE
     Mariam SenbetBeneath the rich history of Ethiopia lies a disturbing trend of violence that has disrupted the tranquility of its ancient monasteries and the well-being of its inhabitants. On February 22, 2024, a brutal assault resulted in the deaths of four monks within the sacred confines of...
    June-23 - 2024 | More »
  • More details emerging about ethnic Amhara Generals led public meeting in Addis
     On Friday, the Ethiopian Defense Force shared a brief update on its social media page about the meeting that the Deputy Chief of Staff, Abebaw Tadesse,  Defense Operations Manager, General  General Belay Seyoum, and Federal Police Deputy Commissioner, Zelalem Mengiste had with...
    June-23 - 2024 | More »
  • Dr. Fisseha Eshetu’s Claims Under Scrutiny: A Closer Look
     Dr. Fisseha EshetuBy Taye HaileDr. Fisseha Eshetu, the CEO of Purpose Black, has recently made headlines by claiming that he fled Ethiopia out of fear of arrest by the government. He alleges that government agents threatened him and accused him of supporting the group known as Fano. However,...
    June-23 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል ሁለት የጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “በመንግሥት ኃይሎች” ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ
     Bahir Darበአማራ ክልል ምዕራብ እና ምሥራቅ ጎጃም ዞኖች ባለፈው ሳምንት በቀናት ልዩነት ውስጥ ተፈጽሟል በተባሉ ጥቃቶች ከ20 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።ጥቃቶቹ ባለፈው ሳምንት ሰኔ 7 እና 9 ቀራኒዮ እና ጂጋ በተባሉ ከተሞች እንደተፈጸሙ የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ሁለቱም ጥቃቶች የመንግሥት ኃይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ካደረጉ በኋላ ስለመፈጸማቸው ገልጸዋል።እሁድ ሰኔ 9 በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህና...
    June-18 - 2024 | More »
  • ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ
     ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ያቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞች ከእስር ተፈቱ። ዛሬ እና ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ፣ ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው። ሶስቱ ጋዜጠኞች የፌደራል ፖሊስ “ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ በእስር እንዲቆዩ” ማድረጉን በመጥቀስ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት ነበር።...
    June-18 - 2024 | More »
  • Jiga, Ethiopia : Government Forces Reportedly Execute 25 Civilians in Following Ambush Loss
     In the latest string of known extrajudicial executions of civilians, the Ethiopian government soldiers reportedly massacred 25 civilians in Jiga, West Gojam, Amhara region of Ethiopia. Residents and Fano forces from the area have confirmed the incident to Ethiopian News outlets based in...
    June-18 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time