Sunday, July 29, 2018

የአቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ



የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።

የታላቁ ኅዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ። አዲስ አበባ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል በተካሔደው የቀብር ሥነ-ሥርዓት የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ፣ ምክትል ጠቅላይ ምኒስትር ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ሹማምንት ተገኝተዋል።  
ድንገተኛ ዜና ዕረፍታቸው ከተሰማ ጀምሮ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የተፈጠረው ሐዘን እና  ቁጭት አለመብረዱ በመስቀል አደባባይ በተካሔደው የሽኝት መርኃ-ግብር ላይ ታይቷል። በሽኝት መርኃ-ግብሩ ላይ ገዳዮቻቸው ለፍርድ ይቅረቡ የሚሉ በርካታ ድምፆች መሰማታቸውን የአይን ዕማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። አቶ ስመኘው ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም መስቀል አደባባይ አካባቢ በተሽከርካሪያቸው ውስጥ ሞተው መገኘታቸው ከተሰማ በኋላ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ሐዘን ተፈጥሯል። ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ የምኅንድስና ባለሙያው አቶ ስመኘው በቀለ የሞት "ዜና ልብ ይሰብራል" ሲሉ ተናግረዋል።
የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።
የ53 አመቱ አቶ ስመኘው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሲቪል ምኅንድስና ያገኙ ሲሆን በግልገል ጊቤ 1 እና ግልገል ጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች መርተዋል። ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ በተባለው ቦታ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የታላቁ ኅዳሴ ግድብ እስከ ዕለተ-ሞታቸው በኃላፊነት ሲመሩ ቆይተዋል።
ከአባታቸው አቶ በቀለ አይናለም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘነቡ አብተው መስከረም 3 ቀን 1957 ዓ.ም. በቀድሞው ጎንደር ልፍለ ሀገር ጠዳ ወረዳ ልዩ ስሙ ማክሰኚት ከተባለ ተወለዱ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በእንፍራንዝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደሴ ቅዳሜ ገበያ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወልዲያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መከታተላቸውን በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተነበበው የሕይወት ታሪካቸው ይጠቁማል።

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time