Thursday, December 28, 2017

በጦርነት እየታመሰች ባለችው የመን ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የሚደርስልን አጣን እያሉ ነው።

በቅርቡ በነበረው ጦርነት በሰንዓ ከተማ ሁለት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጥይት ተመተው እግራቸው ተቆርጧል
በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት የሚደርስልን አጥተን ለእንግልት ተዳርገናል ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
እነዚህ ስደተኞች አብዛኞቹ ሰንዓ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ቢሆንም አሁን ግን በጦርነቱ ምክንያት ወደ ተለያዩ የገጠር አካባቢዎች እየተሰደዱ እንደሆነ እና መፍትሄም እንዳጡ ይናገራሉ።
ጀማል ጄይላን ከ16 ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ወጥቶ በየመን መኖር የጀመረ ሲሆን "ሀገሪቱ በጦርነት እየታመሰች ስለሆነ የሚደርስልን አጥተናል" ይላል።
"ስለዚህ ችግራችንን የምንነግረው አንድም አካል የለም፤ ስንታመም የምንታከምበት ቦታ የለም፤ ብዙ ልጆች ያሏቸው ሰዎች አሉ። ከፍተኛ እንግልት እየደረሰብን ነው" በማለት ያሉበትን ሁኔታ አስረድቷል።
ከዚህ በተጨማሪ "በጦርነቱ ምክንያት ሥራ የለም። ለሰራንበትም ደሞዝ አይከፈለንም፤ ቢከፈለንም ዝቅተኛ ነው። የምግብ ዋጋ ደግሞ እጅጉን ንሯል" ሲል ሁኔታቸውን ይገልፃል።
ሌላኛው ለ17 ዓመት የመን ውስጥ የኖረው ኤርትራዊ እና ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀን ግለሰብ ደግሞ በየመን መንግሥት እና በአማፅያን መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ስደተኞች እየተጎዱ መሆኑን ተናግሯል።
"ሀገሪቱ በጦርነቱ ምክንያት አዲስ ስደተኛ መመዝገብ ካቆመችም ሁለት ዓመት ሆኗታል።"
ስለዚህ ወደ የመን የሚሄዱ ስደተኞች መታወቂያ ከማጣታቸውም በላይ ቀድመው እንኳ መታወቂያውን ያገኙ ማሳደስ አለመቻላቸውን ይናገራል።
አማፅያኑ መግቢያና መውጫ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን ጦርነቱን በመሸሽ ለማምለጥ የሚሞክሩ ስደተኞች ለወታደሮች ጥቃት እየተጋለጡ እንደሆነም ይገልፃል።
በቅርቡ በነበረው ጦርነት እንኳ በሰንዓ ከተማ ጎዳናዎች ሁለት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጥይት ተመተው በደረሰባቸው ጉዳት እግራቸው ተቆርጦ አሁን ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ እንደሆነ ጀማል ይናገራል።
መንገድ ላይ መዘረፍ፣ መታሰር፣ ገንዘብ ከቤተሰብ እንድናስልክ መገደድ እና የመሳሰሉትን ቀድሞም ቢሆን ለምደነዋል፤ የሚለው ኤርትራዊው ስደተኛ በሀገሪቱ ያለው ጦርነት ከመባባሱ ጋር ተያይዞ ግን አንዳንዶች ተገደው ወደ ውትድርና እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ተናግሯል።
ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ማለዳ ላይ በዘጠኝ የሁቲ ፖሊሶች ተደብድቤያለሁ፤ የሚለው አማን መሀመድ መታወቂያውን ቤት ውስጥ ረስቶ መውጣቱን ቢናገርም እንኳ ከከተማዋ ወጣ ባለች የገጠር አካባቢ ወስደው እንደደበደቡት ይናገራል። ከድብደባው በተጨማሪም 330ሺህ የየመን ሪያል መዘረፉንም ይገልፃል።
"ለአንድ ሰው 9 ወታደር ማለት ከባድ ነው። እንደ እባብ ነው የቀጠቀጡኝ። ራሴን እንድስት ከመኪና ጋር አጋጩኝ። ከዚያም ወደ ጦር ሜዳ ሊወስዱኝ ነበር። በኋላም ሁቲዎችን በሚቃወም አንድ ወታደር ነው ነፍሴ ለመትረፍ የቻለው" ይላል አማን።
ኢትዮጵያዊያን፣ ኤርትራዊያን እና ሶማሌያዊያን የስደተኞች ማህበረሰብ አባላት በጋራ በመሆን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የየመኑን ቅርንጫፍ ሄደው ድጋፍ እንዲደረግላቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ይናገራሉ።
የመንImage copyrightMOHAMMED HUWAIS
አጭር የምስል መግለጫየመን ሰነዓ
የቀድሞው ፕሬዝዳንት አሊ አብዱላህ ሳላህ በተገደሉበት ወቅት በሀገሪቱ ያለው ውጥረት ተባብሶ እንደነበር የሚናገሩት እነዚህ ስደተኞች፤ በዚህም ምክንያት የከፋ ችግር ገጥሟቸዋል።
እየደረሰባቸው ያለውንም ችግር ጠቅሰው ኮሚሽኑን እርዳታ ቢጠይቁም አልተዘጋጀንበትም የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው እና በድጋሚ ጥያቄውን አቅርበው ምንም የምናግዛችሁ ነገር የለም የአካል ጉዳት ያለበት ስደተኛ ካልሆነ በቀር በጀት የለንም መባላቸውን ገልፀዋል።
የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ድርጅትም ''የእኛ ድርሻ ጦርነት በተነሳ ወቅት ከጦርነቱ ቀጠና መውጣት ያልቻሉ ሰዎችን ወደ ሰላማዊ ስፍራ መውሰድ ነው'' ማለቱን እነዚሁ ስደተኞች ተናግረዋል።
ስደተኞቹ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የሚገኙበትን ሁኔታ ለዓለም እንዲያሳውቅ ካልሆነ ደግሞ ከየመን መውጣት የሚችሉበትን ሁኔታ እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
የአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ቃል አቀባይ ሊዮናርዶ ዶይል፤ ቀድሞም ቢሆን ፍልሰት መኖሩን ጠቅሰው ከአፍሪካ ቀንድ የሚሰደዱ ግለሰቦች ቀውስ ውስጥ በምትገኝ ሀገር ውስጥ በጦርነት መሃል ይገኛሉ ብለዋል።
"ሰዎችን አትሰደዱ አንልም ነገር ግን በተቻለ መጠን ከወንጀለኛ እና ደላሎች ራሳቸውን ጠብቀው ደህንነቱ የተጠበቀ ስደት እንዲያደርጉ እንፈልጋለን"ብለዋል። Read more here

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopia: 75-Year-Old Civilian Brutally Murdered in Church by Abiy Ahmed Regime’s Forces
     In a shocking and disturbing incident, 75-year-old Mr. Fentaw Derbew, a civilian, was brutally murdered while attending a mass at Kobo Michael Church in Raya Kobo Woreda, North Wollo Zone in Ethiopia. According to eyewitnesses and sources, Mr. Fentaw Derbew was killed by the Abiy Ahmed...
    July-27 - 2025 | More »
  • Ethiopian Health Professionals Association Urges Govt to Promptly Respond to Health Workers' Demands Amid Pre-Strike Demonstrations
     Dagmawi Melnilik Hospital, which was later upgraded to a referral hospital, is the nation’s first hospital, built in 1909.Addis Standard (Addis Ababa)As health professionals across Ethiopia stage pre-strike demonstrations demanding improved salaries, benefits, and working conditions, the...
    May-13 - 2025 | More »
  • Commentary: Why Ethiopian university lecturers' strike failed: A cautionary tale for health professionals
     The moment of release of the detained teachers’ coordinators, greeted by fellow teachers awaiting their return. Photo: Provided by the writerIn 2022, Ethiopian university lecturers launched a year-long social media campaign  and subsequent threat for indefinite...
    May-13 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-08 - 2025 | More »
  • ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ
     የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ...
    May-08 - 2025 | More »
  • በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት
     ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ...
    May-05 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-05 - 2025 | More »
  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው  ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time