Thursday, December 28, 2017

በጦርነት እየታመሰች ባለችው የመን ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የሚደርስልን አጣን እያሉ ነው።

በቅርቡ በነበረው ጦርነት በሰንዓ ከተማ ሁለት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጥይት ተመተው እግራቸው ተቆርጧል
በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት የሚደርስልን አጥተን ለእንግልት ተዳርገናል ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
እነዚህ ስደተኞች አብዛኞቹ ሰንዓ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ቢሆንም አሁን ግን በጦርነቱ ምክንያት ወደ ተለያዩ የገጠር አካባቢዎች እየተሰደዱ እንደሆነ እና መፍትሄም እንዳጡ ይናገራሉ።
ጀማል ጄይላን ከ16 ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ወጥቶ በየመን መኖር የጀመረ ሲሆን "ሀገሪቱ በጦርነት እየታመሰች ስለሆነ የሚደርስልን አጥተናል" ይላል።
"ስለዚህ ችግራችንን የምንነግረው አንድም አካል የለም፤ ስንታመም የምንታከምበት ቦታ የለም፤ ብዙ ልጆች ያሏቸው ሰዎች አሉ። ከፍተኛ እንግልት እየደረሰብን ነው" በማለት ያሉበትን ሁኔታ አስረድቷል።
ከዚህ በተጨማሪ "በጦርነቱ ምክንያት ሥራ የለም። ለሰራንበትም ደሞዝ አይከፈለንም፤ ቢከፈለንም ዝቅተኛ ነው። የምግብ ዋጋ ደግሞ እጅጉን ንሯል" ሲል ሁኔታቸውን ይገልፃል።
ሌላኛው ለ17 ዓመት የመን ውስጥ የኖረው ኤርትራዊ እና ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀን ግለሰብ ደግሞ በየመን መንግሥት እና በአማፅያን መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ስደተኞች እየተጎዱ መሆኑን ተናግሯል።
"ሀገሪቱ በጦርነቱ ምክንያት አዲስ ስደተኛ መመዝገብ ካቆመችም ሁለት ዓመት ሆኗታል።"
ስለዚህ ወደ የመን የሚሄዱ ስደተኞች መታወቂያ ከማጣታቸውም በላይ ቀድመው እንኳ መታወቂያውን ያገኙ ማሳደስ አለመቻላቸውን ይናገራል።
አማፅያኑ መግቢያና መውጫ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን ጦርነቱን በመሸሽ ለማምለጥ የሚሞክሩ ስደተኞች ለወታደሮች ጥቃት እየተጋለጡ እንደሆነም ይገልፃል።
በቅርቡ በነበረው ጦርነት እንኳ በሰንዓ ከተማ ጎዳናዎች ሁለት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጥይት ተመተው በደረሰባቸው ጉዳት እግራቸው ተቆርጦ አሁን ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ እንደሆነ ጀማል ይናገራል።
መንገድ ላይ መዘረፍ፣ መታሰር፣ ገንዘብ ከቤተሰብ እንድናስልክ መገደድ እና የመሳሰሉትን ቀድሞም ቢሆን ለምደነዋል፤ የሚለው ኤርትራዊው ስደተኛ በሀገሪቱ ያለው ጦርነት ከመባባሱ ጋር ተያይዞ ግን አንዳንዶች ተገደው ወደ ውትድርና እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ተናግሯል።
ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ማለዳ ላይ በዘጠኝ የሁቲ ፖሊሶች ተደብድቤያለሁ፤ የሚለው አማን መሀመድ መታወቂያውን ቤት ውስጥ ረስቶ መውጣቱን ቢናገርም እንኳ ከከተማዋ ወጣ ባለች የገጠር አካባቢ ወስደው እንደደበደቡት ይናገራል። ከድብደባው በተጨማሪም 330ሺህ የየመን ሪያል መዘረፉንም ይገልፃል።
"ለአንድ ሰው 9 ወታደር ማለት ከባድ ነው። እንደ እባብ ነው የቀጠቀጡኝ። ራሴን እንድስት ከመኪና ጋር አጋጩኝ። ከዚያም ወደ ጦር ሜዳ ሊወስዱኝ ነበር። በኋላም ሁቲዎችን በሚቃወም አንድ ወታደር ነው ነፍሴ ለመትረፍ የቻለው" ይላል አማን።
ኢትዮጵያዊያን፣ ኤርትራዊያን እና ሶማሌያዊያን የስደተኞች ማህበረሰብ አባላት በጋራ በመሆን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የየመኑን ቅርንጫፍ ሄደው ድጋፍ እንዲደረግላቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ይናገራሉ።
የመንImage copyrightMOHAMMED HUWAIS
አጭር የምስል መግለጫየመን ሰነዓ
የቀድሞው ፕሬዝዳንት አሊ አብዱላህ ሳላህ በተገደሉበት ወቅት በሀገሪቱ ያለው ውጥረት ተባብሶ እንደነበር የሚናገሩት እነዚህ ስደተኞች፤ በዚህም ምክንያት የከፋ ችግር ገጥሟቸዋል።
እየደረሰባቸው ያለውንም ችግር ጠቅሰው ኮሚሽኑን እርዳታ ቢጠይቁም አልተዘጋጀንበትም የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው እና በድጋሚ ጥያቄውን አቅርበው ምንም የምናግዛችሁ ነገር የለም የአካል ጉዳት ያለበት ስደተኛ ካልሆነ በቀር በጀት የለንም መባላቸውን ገልፀዋል።
የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ድርጅትም ''የእኛ ድርሻ ጦርነት በተነሳ ወቅት ከጦርነቱ ቀጠና መውጣት ያልቻሉ ሰዎችን ወደ ሰላማዊ ስፍራ መውሰድ ነው'' ማለቱን እነዚሁ ስደተኞች ተናግረዋል።
ስደተኞቹ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የሚገኙበትን ሁኔታ ለዓለም እንዲያሳውቅ ካልሆነ ደግሞ ከየመን መውጣት የሚችሉበትን ሁኔታ እንዲያመቻች ጠይቀዋል።
የአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ቃል አቀባይ ሊዮናርዶ ዶይል፤ ቀድሞም ቢሆን ፍልሰት መኖሩን ጠቅሰው ከአፍሪካ ቀንድ የሚሰደዱ ግለሰቦች ቀውስ ውስጥ በምትገኝ ሀገር ውስጥ በጦርነት መሃል ይገኛሉ ብለዋል።
"ሰዎችን አትሰደዱ አንልም ነገር ግን በተቻለ መጠን ከወንጀለኛ እና ደላሎች ራሳቸውን ጠብቀው ደህንነቱ የተጠበቀ ስደት እንዲያደርጉ እንፈልጋለን"ብለዋል። Read more here

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ ሃገራት ሰዎች...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል በዚህ ሳምንት ከ27 በላይ የሚሆኑ ‘ሰላማዊ ሰዎች’ “በመንግሥት ኃይሎች” መገደላቸው ተነገረ
     በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “የመንግሥት ኃይሎች” ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።የደብረሲና ከተማጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19፤ 2016 ዓ/ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን፤ በጥቃቶቹም ከ27 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር...
    June-29 - 2024 | More »
  • AMHARA MASSACRE: A GRIM REMINDER OF ETHIOPIA’S FRAGILE PEACE
     Mariam SenbetBeneath the rich history of Ethiopia lies a disturbing trend of violence that has disrupted the tranquility of its ancient monasteries and the well-being of its inhabitants. On February 22, 2024, a brutal assault resulted in the deaths of four monks within the sacred confines of...
    June-23 - 2024 | More »
  • More details emerging about ethnic Amhara Generals led public meeting in Addis
     On Friday, the Ethiopian Defense Force shared a brief update on its social media page about the meeting that the Deputy Chief of Staff, Abebaw Tadesse,  Defense Operations Manager, General  General Belay Seyoum, and Federal Police Deputy Commissioner, Zelalem Mengiste had with...
    June-23 - 2024 | More »
  • Dr. Fisseha Eshetu’s Claims Under Scrutiny: A Closer Look
     Dr. Fisseha EshetuBy Taye HaileDr. Fisseha Eshetu, the CEO of Purpose Black, has recently made headlines by claiming that he fled Ethiopia out of fear of arrest by the government. He alleges that government agents threatened him and accused him of supporting the group known as Fano. However,...
    June-23 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል ሁለት የጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “በመንግሥት ኃይሎች” ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ
     Bahir Darበአማራ ክልል ምዕራብ እና ምሥራቅ ጎጃም ዞኖች ባለፈው ሳምንት በቀናት ልዩነት ውስጥ ተፈጽሟል በተባሉ ጥቃቶች ከ20 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።ጥቃቶቹ ባለፈው ሳምንት ሰኔ 7 እና 9 ቀራኒዮ እና ጂጋ በተባሉ ከተሞች እንደተፈጸሙ የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ሁለቱም ጥቃቶች የመንግሥት ኃይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ካደረጉ በኋላ ስለመፈጸማቸው ገልጸዋል።እሁድ ሰኔ 9 በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህና...
    June-18 - 2024 | More »
  • ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ
     ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ያቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞች ከእስር ተፈቱ። ዛሬ እና ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ፣ ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው። ሶስቱ ጋዜጠኞች የፌደራል ፖሊስ “ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ በእስር እንዲቆዩ” ማድረጉን በመጥቀስ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት ነበር።...
    June-18 - 2024 | More »
  • Jiga, Ethiopia : Government Forces Reportedly Execute 25 Civilians in Following Ambush Loss
     In the latest string of known extrajudicial executions of civilians, the Ethiopian government soldiers reportedly massacred 25 civilians in Jiga, West Gojam, Amhara region of Ethiopia. Residents and Fano forces from the area have confirmed the incident to Ethiopian News outlets based in...
    June-18 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time