Sunday, July 29, 2018

የአቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ



የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።

የታላቁ ኅዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ። አዲስ አበባ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል በተካሔደው የቀብር ሥነ-ሥርዓት የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ፣ ምክትል ጠቅላይ ምኒስትር ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ሹማምንት ተገኝተዋል።  
ድንገተኛ ዜና ዕረፍታቸው ከተሰማ ጀምሮ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የተፈጠረው ሐዘን እና  ቁጭት አለመብረዱ በመስቀል አደባባይ በተካሔደው የሽኝት መርኃ-ግብር ላይ ታይቷል። በሽኝት መርኃ-ግብሩ ላይ ገዳዮቻቸው ለፍርድ ይቅረቡ የሚሉ በርካታ ድምፆች መሰማታቸውን የአይን ዕማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። አቶ ስመኘው ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም መስቀል አደባባይ አካባቢ በተሽከርካሪያቸው ውስጥ ሞተው መገኘታቸው ከተሰማ በኋላ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ሐዘን ተፈጥሯል። ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ የምኅንድስና ባለሙያው አቶ ስመኘው በቀለ የሞት "ዜና ልብ ይሰብራል" ሲሉ ተናግረዋል።
የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።
የ53 አመቱ አቶ ስመኘው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሲቪል ምኅንድስና ያገኙ ሲሆን በግልገል ጊቤ 1 እና ግልገል ጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች መርተዋል። ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ በተባለው ቦታ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የታላቁ ኅዳሴ ግድብ እስከ ዕለተ-ሞታቸው በኃላፊነት ሲመሩ ቆይተዋል።
ከአባታቸው አቶ በቀለ አይናለም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘነቡ አብተው መስከረም 3 ቀን 1957 ዓ.ም. በቀድሞው ጎንደር ልፍለ ሀገር ጠዳ ወረዳ ልዩ ስሙ ማክሰኚት ከተባለ ተወለዱ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በእንፍራንዝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደሴ ቅዳሜ ገበያ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወልዲያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መከታተላቸውን በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተነበበው የሕይወት ታሪካቸው ይጠቁማል።

Thursday, July 26, 2018

Who killed Engineer Simegnew & why? (just asking)

Who killed Engineer Simegnew & why? (just asking)
State-owned Ethiopian Electric Power ( # EEP ) has failed to produce a detailed financial report for the last two years.
The problems are partly due to the weaknesses of a bloated and hierarchical utility company. Decision-making at EEP is sluggish and there are not enough empowered managers, according to individuals who work with the corporation. EEP executives are over-burdened and lack technical expertise. One consultant said even decisions to purchase cables now have to get board approval because of a lack of trust in the management. A donor representative said EEP has failed to produce a detailed financial report for the last two years. Such issues are typical of Ethiopia’s public sector, which is weakened by meager salaries, places a premium on political loyalty, and is partly an ethnic balancing act when it comes to senior appointments.
#Military_Power
Politics is also relevant at the top of an industry where veterans of the armed struggle exert considerable influence. EEP’s board is chaired by
#Debretsion_Gebremichael , a minister who was a leading engineer for the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) during the 17-year rebellion that ended with the Derg regime crumbling in 1991. The originally Leninist TPLF formed the core of the revamped military and founded the revolutionary ruling coalition that still dominates Ethiopian politics.
Debretsion oversees the # GERD, whose electro-mechanical works were contracted to a conglomerate run by military officers. Lacking the requisite experience, that group, the Metals and Engineering Corporation ( #METEC ), sub-contracted turbine construction to France’s Alstom and Germany’s Voith Hydro. While a foreign adviser says METEC’s role in the GERD has not caused problems, it has failed to deliver seperate sugar and fertilizer factories on time while pocketing substantial payments in advance. For years the ruling coalition has identified surging corruption as the primary domestic threat to realizing Meles’ development vision.
In an interview with The Reporter newspaper in March, Debretsion bullishly defended METEC’s role, arguing it helped stave off foreign pressure to downsize the GERD and was necessary to build domestic industrial capacity. He was also positive about the prospects for private investment in Ethiopian energy projects. But such views demonstrate the conundrums for Addis Ababa’s policy makers: despite the need for foreign capital, there are long-held suspicions from Marxist-influenced politicians about private profiteering; and the effort to rapidly boost energy production is sometimes at odds with aspirations to improve local engineering capabilities.
According to one energy consultant, these attitudes are a major obstacle to sustaining Ethiopia’s impressive momentum in the power sector, especially when it comes to facilitating the development of privately owned power plants. “There is still a question of whether at the highest level of the government they understand what an IPP is. It could have exploded with development if the right people were managing the economy,” the consultant said.
By William Davison

Thursday, July 19, 2018

መንግሥት በዶላር ጉዳይ መግለጫ ሰጠ


በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ትእዛዝ መሰረት በርካቶች በእጃቸው ያለውን የውጭ ሀገር ገንዘብ ወደ ባንክ እያስገቡ መሆኑን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የውጭ ምንዛሪ በእጃቸው የያዙ አካላት በፍጥነት ወደ ባንክ ገቢ እንዲያደርጉ ባሳለፍነው ሰኞ ሐምሌ 9 2010 በሰጡት መግለጫ ማሳሰባቸው ይታወሳል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በወቅቱም፥ የውጭ ምንዛሪውን ያከማቹ አካላት በእጃቸው ያለውን ገንዘብ በፍጥነት ወደ ንግድ ባንኮች ገቢ በማድረግ ከኪሳራ እንዲድኑም ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጥሪ ማቅረባቸውን አስታውሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሪ
ተከትሎም በርካቶች በእጃቸው ያለውን የውጭ ሀገር ገንዘብ ወደ ባንክ እያስገቡ ነው ብለዋል።
በዚህም በጥቁር የውጭ ምንዛሪ ገበያ ሲዘዋወር የነበረው አብዛኛው ገንዘብ ወደ ተለያዩ የንግድ ባንኮች እየመጣ መሆኑን የገለጹት አቶ አህመድ፥ የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ክምችትም እየጨመረ መጥቷል ነው ያሉት።
ህብረተሰቡ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ጥሪ በዚህ ፍጥነት ምላሽ በመስጠቱም የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳይ ሀላፊ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
አቶ አህመድ አክለውም፥ አሁንም የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘብን በተለያየ መልኩ ያከማቹ ሰዎች በአፋጣኝ ወደ ባንክ እንዲወስዱ 
አሳስበዋል። የውጭ ምንዛሬ የጥቁር ገበያን ለማዳከም በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም አቶ አህመድ ሽዴ በመግለጫቸው ተናግረዋል።
ከሚሰወዱት እርምጃዎች ጎን ለጎንም ከወዳጅ ሀገሮች እና ተቋማት በልማት ፋይናንስ መልክ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የውጭ ምንዛሪ ለማሳደግ የተሰራው ስራም ውጤታማ መሆኑን ገልፀዋል።
መንግስት ህብረተሰቡን ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው ተጠቃሚ ለማድረግ አዳዲስ የፖሊሲ አቅጣጫዎች መያዛቸውንም አቶ አህመድ ሽዴ በመግለጫቸው አብራርተዋል።
በዚህም መሰረት በመንግስት የልማት ድርጅት ስር የሚገኙ አራት ድርጅቶችን አብዛኛውን ድርሻ መንግስት ይዞ ቀሪው ድርሻ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ባለሀብቶች እንዲተላለፉ መወሰኑን ገልፀዋል።
ሌሎች የመንግስት የልማት ድርጅቶችም ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ወደ ግል እንዲዘዋወሩ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም አቶ አህመድ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።
ይህ የሚሆንበት ዋናው ምክንያትን በሀገሪቱ እየተመዘገበ የመጣውን ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠል ነው ሲሉም አቶ አህመድ አብራርተዋል።
በተጨማሪም የግሉ ሴክተር በኢኮኖሚው ላይ ያለውን ሚና ለማሳደግ እና ዓለም አቀፍ እንቨስትመንትን ወደ ኢትዮጵያ ለመሳብ ያለመ መሆኑንም ገልፀዋል።
ምንጭ መንግስት ጉዳዮች ኮሙኒኬሽን

Wednesday, July 11, 2018

በአሁኑ ወቅት የኦሮሞ ነፃ አውጪ ነኝ በሚል ስም የጦርነት አዋጅ እያወጀ ያለው አካል ፣ እያደረገ ያለው ነገር እንዲያስብበት እና ወደትክክለኛው መንገድ እንዲመለስ ኦቦ ለማ መገርሳ አስጠነቀቁ

በአሁኑ ወቅት የኦሮሞ ነፃ አውጪ ነኝ በሚል ስም የጦርነት አዋጅ እያወጀ ያለው አካል ፣ እያደረገ ያለው ነገር እንዲያስብበት እና ወደትክክለኛው መንገድ እንዲመለስ ኦቦ ለማ መገርሳ አስጠነቀቁ። የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦቦ ለማ መገርሳ የጦርነት አዋጅ ያወጀውን ቡድን ያስጠነቀቁት፣ ትናንት በኦሮሚያ ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር ነው። “ከዚህ በፊት ቀጥታ ሲዋጉን የነበሩ አካላት ዛሬ ስፓንሰር በመሆንና ገንዘባቸውን በመርጨት የክልሉት ፀጥታ ለማደፍረስ እንቅልፍ አጥተው እየሰሩ ይገኛሉ ያሉት አቅቶ ለማ፣ ከስፓንሰሮቹ የሚለገሳቸውን ገንዘብ በመቀበል የተሰጣቸውን ተልዕኮ ለማስፈፀም ዝግጁ የሆኑ በርካታ የእኛው ወንድሞችም በመከላችን ይገኛሉ” ብለዋል፡፡ “ለዚህ ህዝብ ሁላችንም እንሥራለት በሚል ውሳኔ ሁሉም ወደ ሀገር ተመልሶ በሀሳብ በመፋለም አንድ ላይ መስራት አለብን ብለን ጥሪ ከማድረግም በላይ ፣ ህዝባችንን አምነን ብዙዎቹን ከሰሩት ወንጀልም ነፃ እንዲሆኑ አደረግን “ ያሉት ር ዕሰ መስተዳድሩ፣ የፓለቲካ ታርጋ ተለጥፎባቸው በሰው ሀገር የተበተኑ ወገኖቻችን ተመልሰው ለሀገር እንዲሰሩ በራፉን በከፈትንበት ፣ ብዙዎች ጥሪዎን ተቀብለው እየገቡ ባለበት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን እየፈታን ባለንበት እና አጠቃላይ የፓለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ ባለበት ጊዜ ፣”አይ! የኦሮሞ ነፃነትን ለማስከበር ትክክለኛ የጦርነት መክፈቻው ጊዜ አሁን ነው” ተብሎ በኦሮሞ ህዝብ ስም የሚደረግ እንቅስቃሴ ትርጉሙ ምን እንደሆነ በግሌ አልገባኝ”ብለዋል። አቶ ለማ አክለውም፦”ለኦሮሞ ነፃነት ለማስከበር የሚያስቡ ከሆነ ፣እስከዛሬ ይሄን ሁሉ ዘመን የት ነበሩ?…ሲሉ ጠይቀዋል። . “ እነዚህ ወገኖች ከልጅ ፊት አባት ገድለው ሬሳውን አቃጥለዋል።ሬሳ በማቃጠል የህዝብ ነፃነት እንዴት መከበር እንደሚችል አላውቅም። ኦሮሞ-ኦሮሞን ነው እየገደለው ያለው።…በምዕራብ ኦሮሚያ እየሆነ ያለው ነገር ይሄ ነው፡፡” ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አክለዋል። “ቄሮ ለዓመታት በመሪነት ባደረገው ትግልና በከፈለው መስዋዕትነት አሁን እያየነው ያለነው ለውጥ እንዲመጣ እና ዛሬ የመጣውን ውጤት እንድንጎናፀፍ አድርጎል.” ያሉት ኦቦ ለማ መገርሳ፣ “ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በቄሮ ስም ለመነገድ የሚሞክሩ ወጣቶች እዚህም እዛም የመዝረፍና አንዳንድ አካባቢዎችን የማወክ አዝማሚያ እያሳዩ እንደሆነ አልሸሸጉም። “ቄሮዎች ግን ይሄ በታሪክ ማህደር ላይ የተከተበ የጀግንነትና ለህዝብ መስዋዕትነት የከፈሉት ደማቸው ባክኖ እንዲቀርባቸው ስለማይፈልጉ፣ አሁንም እነዚህን ቅጥረኞች አደብ በማስገዛት እና ወደመስመር በማስገባት ረገድ ትልቅ ምሳሌ የሚሆን ስራ በመስራ ላይ ይገኛሉ”ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ “ህዝባችንም እንደዛው እያደረገ ነው፡ብለዋል። ይህ ሕግን የማስከበርና ሰላምና መረጋጋትን የማረጋገጥ ተግባር በሁሉም አካባቢ ተጠናክሮና ተስፋፍቶ መተግበር እንዳለበትም አቶ ለማ አሣስበዋል፡፡ “በአሁኑ ወቅት በክልላችን መዋቅር ውስጥ እንደ ኦሮሚያ ፖሊስ ለህዝቡ ዋልታና መከታ የሆነ አካል አኔ በግሌ አላውቅም” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በዛ በጭንቀትና በመከራ እና አይዟችሁ የሚለን ባጣንበት ጊዜ ከጎናችን ቆሞ ደሙን እያዛራ እና ህይወቱን እየሰጠ ለዚህ ለዛሬው ቀን እንደንደርስ የሚችለውን ሁሉ ያደረገ የህዝብ አካል ነው”ብለዋል። አቶ ለማ አክለውም፦”የኦሮሚያ ፓሊሶች ለሚከፈላቸው ደሞዝ አየይደለም ፋቲኩን የለበሱት፡፡ እኔ እንደ ኦሮሚየ ፓሊስ በቁርጠኝነት ለህዝብ የቆመ አላውቅም።ቁርስ በልቶ ምሳ ሳይደግም ፀሀይና ንፋስ እየተፈራረቀበት መካራውን በማየት ከገዛ ስንቁ ለህዝቡ እየቀነሰ ሲሰቃይ የነበረ የህዝብ ወገን ነው።ለህዝባቸው ሲሉ ቤተሰባቸውን በትነው በየቆላውና በየድንበሩ በርካቶቹ ህይወታቸውን አጥተዋል። …. ታዲያ እንዴት ዛሬ በኦሮሚያ ፓሊስ ላይ ልክ እንደህዝብ ጠላት ቦንብ ይጣልበታል…? ይህ ፖሊስ እንዴት ዛሬም ይገደላል……?ምን ተፈልጎ ነውአሁን አንዳችን በሌላችን ላይ ቂም እንድናወጣ ጥሪ እየተደረገ ያለው?”ሲሉ በአጽንዖት ጠይቀዋል። “ኦሮሚያ ውስጥ አናርኪ ለመፍጠር ገንዘብ በመርጨት የሚሰራ ስራ አለ ። እንስራለን ብለን ያቀድነውን ስራ ትተን ሌላውን ስራ እድንሰራ ነው እየተፈለገ ያለው” ያሉት አቶ ለማ፣ …ዛሬም ችግሮች ቢኖሩም ቄሮዋች ከጎናችን ሆነው እየታገሉ ናቸው “ብለዋል። አሁንም የኦሮሞ ነፃ አውጪ በሚል ስም የጦርነት አዋጅ እያወጀ ያለው አካል ድርጊቱን ቆም ብሎ እንዲያስቡበት እና ወደትክክለኛው መንገድ እንዲመለስ የመከሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ይሄን ያሉት ለመንግስት ችግሩን መቆጣጠር ከባድ ሆኖበት ሳይሆን ወዳልተፈለገ የኃይል እርምጃ ከመግባት ይልቅ ጉዳዩ በሰላም እልባት እንዲያገኝ ካላቸው ፍላጎት በመነሳት እንደሆነ አብራርተዋል።ኦቦ ለማ መገርሳ ንግግራቸውን ሲቋጩም፦”ጭቆና መሸከም አንችልም ብለን ታግለንና መስዋእትነት ከፍለን ወደ ነጻነት መንገድ መሸጋገር ጀምረናል..ዛሬስ ነፃነትንም መሸከም የማንችል ህዝቦች ነን እንዴ..?”ሲሉ ጠይቀዋል።
Esat

Monday, July 9, 2018

Eritrea and Ethiopia have signed a Joint Declaration of Peace and Friendship


Eritrea and Ethiopia have signed a Joint Declaration of Peace and Friendship.
The Agreement, which specifies five pillars, was signed this morning at State House by President Isaias Afwerki and Prime Minister Abiy Ahmed
Joint Declaration states, inter alia,
I) State of war that existed between the two countries has come to an end. A new era of peace & friendship has been ushered;
II) Both countries will work to promote close cooperation in political, economic, social, cultural & security areas
III) Transport, trade and telecommunication ties will be resumed; diplomatic ties & activities renewed;
IV) Border decision will be implemented;
V) Both countries will work together to guarantee regional peace, development & cooperation
(Source: Yemane Gebremeskel tweeter, an Eritrean authority)
Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time