Tuesday, June 18, 2024

በአማራ ክልል ሁለት የጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “በመንግሥት ኃይሎች” ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ

 

Bahir Dar

በአማራ ክልል ምዕራብ እና ምሥራቅ ጎጃም ዞኖች ባለፈው ሳምንት በቀናት ልዩነት ውስጥ ተፈጽሟል በተባሉ ጥቃቶች ከ20 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጥቃቶቹ ባለፈው ሳምንት ሰኔ 7 እና 9 ቀራኒዮ እና ጂጋ በተባሉ ከተሞች እንደተፈጸሙ የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ሁለቱም ጥቃቶች የመንግሥት ኃይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ካደረጉ በኋላ ስለመፈጸማቸው ገልጸዋል።

እሁድ ሰኔ 9 በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህና ወረዳ ጂጋ ከተማ በተፈጸመው ጥቃት መምህራን እና የባንክ ቤት ሠራተኞችን ጨምሮ በርካታ ሰዎች “መረሸናቸውን” ሁለት የዐይን እማኞች እና ከተማዋን ወክለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የገቡት አቶ አበባው ደሳለው ተናግረዋል።

አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የዐይን እማኝ ከግድያው በፊት በከተማዋ ደምበጫ በር የሚባል ሰፈር አካባቢ ለ20 ደቂቃ ያህል የቆየ ውጊያ በፋኖ እና በመከላከያ ሠራዊት መካከል መደረጉን ጠቁመዋል።

ሌላ የዐይን እማኝም እንዲሁ፤ “ከደንበጫ ወደ ጂጋ የሚመጣ ሦስት ፓትሮል ነበር። የፋኖ አባላት ጥቁር ውሃ ከሚባል አካባቢ የደፈጣ ጥቃት አደረሱ” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ሃያ ደቂቃ ከቆየው የተኩስ ልውውጥ በኋላ የፋኖ ታጣቂዎች ወደ ኋላ ማፈግፈጋቸውን የተናገሩት ነዋሪው፤ ከፋኖ ማፈግፈግ በኋላ “የመከላከያ ሠራዊት አባላት በበቀል” ነዋሪዎችን መግደላቸውን አክለዋል።

ግድያው ከተፈጸመበት ቦታ በቅርብ ርቀት ላይ እንደነበሩ የተናገሩ የዐይን እማኝ፤ “ጎህ የሚባል ሆቴል ላይ ወጣቶች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ የባንክ ሠራተኞችን [እና] መምህራንን [በድምሩ] 12 ሰዎችን አውጥተው በሕዝብ ፊት በአስቃቂ ሁኔታ ገደሏቸው” ሲሉ የተመለከቱትን ክስተት ለቢቢሲ ገልጸዋል።

ሁለተኛው የአካባቢ ነዋሪም በተመሳሳይ “የመከላከያ ሠራዊት መስመር ላይ ያገኘውን ጎህ የሚባል ሆቴል እራት ለመብላት የገቡትን ባንክ ቤት ሠራተኞች፤ መምህራን ያገኙት በሙሉ ረሸኑ” ብለዋል።

ሁለቱም ነዋሪዎቹ በጂጋ ከተማ የምትኖር አንዲት የአዕምሮ ህመምተኛን ጨምሮ “12 ሰዎች በመከላከያ ሠራዊት ሲገደሉ” መመልከታቸውን እና ከተመለከቱትን ጨምሮ በድምሩ 23 ሰዎች ተገድለዋል ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ሌሎች ሁለት ግለሰቦች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ከምዕራብ ጎጃም ዞን ጂጋ ምርጫ ክልልን ወክለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አበባው ደሳለው በበኩላቸው፤ “እስካሁን ስም ዝርዝራቸው እና ሥራቸው በእጃችን የደረሰ 13 ሟቾች አሉ፤ ሁለት ደግሞ የቆሰሉ ናቸው” ሲሉ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

የምክር ቤት አባሉ አክለውም “ተጨማሪ የሟቾች ዝርዝር ይመጣል ብለን ነው የምንጠብቀው፤ የተረጋገጠ ግን የ13 ሟቾች እና የሁለት ቁስለኞች ዝርዝር አለን” ብለዋል።

“ተዋጊ ኃይሎች እርስ በእርስ ሊገዳደሉ ይችላሉ። አምነው የገቡበት ነው። የጦርነት ጨዋታ ነው እሱ። ነገር ግን ምንም ያልታጠቁ ንጹሃንን ከቤታቸው እያወጡ መረሸን አግባብነት የለውም” ብለዋል የምክር ቤት አባሉ።

አቶ አበባው አክለውም እሁድ ዕለት የተፈጸመውን ክስተት በተመለከት ለሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለኤምባሲዎች በደብዳቤ እንደሚያሳውቁ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል በምሥራቅ ጎጃም ዞን ሁለት እጁ እነሴ ወረዳም አርብ ሰኔ 7/2016 ዓ.ም. “በመንግሥት ኃይሎች” ተፈጽሟል በተባለ ጥቃት የሰባት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ሁለት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ነዋሪዎች እና የዐይን እማኞች ተናግረዋል።

ጥቃቱ ከወረዳው ዋና ከተማ ሞጣ በ16 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው ቀራኒዮ አነስተኛ ከተማ ‘ደብረ ቀራኒዮ መድኃኒያለም ቤተ-ክርስቲያን’ ቅጥር ግቢ ውስጥ ለቀብር ጉድጓድ ሲቆፍሩ ነበሩ የተባሉ እድርተኞች ላይ መፈጸሙን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ጥቃቱ ከመፈጸሙ አስቀድሞ በአካባቢው የመንግሥት ኃይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች የተኩስ ልውውጥ እያደረጉ እንደነበር የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ጥቃቱ ተኩሱ ጋብ ማለቱን ተከትሎ ጠዋት 3፡00 ላይ መፈጸሙን አመልክተዋል።

የቤተ-ክርስቲያኒቷ አገልጋይ የሆኑ አንድ የዐይን እማኝ ተፋላሚ ኃይሎቹ ተኩስ ልውውጥ ማድረግ ሲጀምሩ ወደ ቤተ-ክርስቲያን ውስጥ መግባታቸውን ገልጸው፤ መቃብር ሲቆፍሩ የነበሩ እድርተኞች ግን ቁፋሮ ላይ እያሉ እርሳቸው “መከላከያ” ባሏቸው ኃይሎች ስለመገደላቸው ገልጸዋል።

የመንግሥት ኃይሎች መጠጋታቸውን ተከትሎ “የሥላሴ ቅዳሴ” ላይ የነበረው ምዕመን ወደ ቤተ-ክርስቲያን ውስጥ እንዲገባ ማድረጋቸውን የተናገሩት አገልጋዩ፤ መቃብር ቆፋሪዎቹ ግን “‘እኛ መቃብር ነው የምንቆፍረው ንጹሃን ነን፤ ምንም አንሆንም’ ብለው ሲቆፍሩ” የጥቃቱ ሰለባ እንደሆኑ እማኝነታቸውን ተናግረዋል።

“የሆነች ሴትዮ ሞታ ኑሯል፤ ሕዝቡ ተሰባስቦ የባለእግዚያብሔር እድር ነበር የእሷን መቃብር እየቆፈሩ ነው [ጥቃቱ የደረሰው]። እንዲያ ሲታኮሱ ቆይተው መጥተው ሲያያቸው [መቃብር ቆፋሪዎቹን] ምን እንዳሰቡ እንጃ እዳሪ [ከመቃብር ቤት ውጭ] ያሉትንም፤ ቤት ያሉትንም ገድለዋቸው ነው የሄዱት” ሲሉ ስለ ግድያው ተናግረዋል።

ሌላ ነዋሪም አንድ በእድሜ የገፉ መነኩሴን ለመቅበር መቃብር እየቆፈሩ የነበሩ እድርተኞች ላይ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጸዋል።

አምስቱ ሰዎች ወዲያውኑ ሕይታቸው ሲያልፍ፤ አንዱ ሆስፒታል ከሄደ በኋላ እንዲሁም አንድ የቆሎ ተማሪ ደግሞ ከቤተ-ክርስቲያን ወጣ ባለ አካባቢ ተገድሎ መገኘቱን ተናግረዋል።

ጥቃቱን “አሰቃቂ ጭፍጨፋ” ሲሉ የገለጹት የአካባቢው ነዋሪ፤ አስከሬን ለማንሳት ወዲያው ወደ ቤተ-ክርስቲያኒቷ ቅጥር ጊቢ መድረሳቸውን ተናግረዋል።

“ስንሄድ አምስት ሰዎች አንድ ላይ ተገድለዋል። ስድስተኛው የሞተው በኋላ ላይ ነው። ጭንቅላቱ አካባቢ ላይ ነው የተመታው። ስለዚህ ነፍስ ስለነበረው እሱን ለማዳን ቅድሚያ ለእሱ ትኩረት ሰጥተን አነሳነው” ብለዋል።

ሦስት ሰዎች ቆስለው ቀራኒዮ ጤና ጣቢያ ለህክምና መግባታቸውን ለቢቢሲ ያረጋገጡ አንድ የህክምና ባለሙያ፤ ጭንቅላቱ ላይ የቆሰለው ታካሚ ሕይወቱ ከሰዓት በኋላ ማለፉን ገልጸዋል።

“ሁለቱ እጃቸውን፤ አንዱ ጭንቅላቱን ነው የተመታው። ለሞጣ ሪፈር ብለነው [ጭንቅላቱን የተመታው] ሞጣ ሲደርስ ሕይወቱ አለፈ” ሲሉ የህክምና ተቋም ምንጩ ተናግረዋል።

የጥቃቱ ሰለባዎች በጉልበት ሥራ ይተዳደሩ የነበሩ ሰዎች መሆናቸውን የተናገሩት ነዋሪዎች እድርተኛ በመሆናቸው ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ቁፋሮ ላይ የነበሩ መሆናቸውን አመልክተዋል።

“በአብዛኛው ደካማ [ኑሮ የሚኖሩ]፣ እንጨት የሚፈልጡ፣ ረዳት ሆነው ቋጠሮ የሚሸከሙ፣ ጭቃ የሚያቦኩ ሰዎች ናቸው የተገደሉት” ሲሉ አንድ ነዋሪ ስለ ሟቾቹ ማንነት ተናግረዋል።

የመንግሥት ኃይሎች “ምሽግ ትቆፍራላችሁ” በሚል ጥርጣሬ ግድያውን እንደተፈጸሙ አስከሬን ተጭኗቸው በሕይወት መትረፍ ከቻሉ ሰዎች መረዳታቸውን የደብሩ አገልጋይ ተናግረዋል።

ጥቃት አድራሹ “መከላከያ” ለመሆኑ በምን እርግጠኛ እንደሆኑ ለቢቢሲ የተናገሩት ነዋሪዎች፤ በለበሱት የደንብ ልብስ፣ በሚያሽከረክሩት መኪና እንዲሁም በአካባቢው ሲንቀሳሰቀሱ የሚያውቋቸው በመሆናቸው እንደሆነ ገልጸዋል።

የሟቾቹ ቀብር የዚያኑ ቀን መፈጸሙን ነዋሪዎች የተናገሩ ሲሆን፤ አምስቱ ሰዎች በአንድ ጉድጓድ ውስጥ መቀበራቸውን ተናግረዋል።

“. . . ተመልሰው መጥተው ይመቱናል የሚል ስጋት ነበር። ‘ይመለሳሉ፤ አሁን መጡ’ የሚል ስጋትም ነበር” በማለት በአንድ ጉድጓድ ለመቅበር መገደዳቸውን ገልጸዋል።

ጥቃቱን ተከትሎ በአካባቢው ስጋት ማደሩን የተናገሩት ነዋሪዎች፤ በቀራኒዮ የገበያ ቀን የሆነውን ቅዳሜን ጨምሮ ግብይትና እንቅስቃሴ እንደሌለ ተናግረዋል።

አንድ ዓመት ሊሞላው በተቃረበው የአማራ ክልል አለመረጋጋት፣ በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚካሄዱ ግጭቶች ሰላማዊ ሰዎች ሰለባ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ የተለያዩ የመብት ተቋማት የሚያወጧቸው ሪፖርቶች ያመለክታሉ።

Source: https://www.bbc.com/amharic/articles/cg33wypl722o

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ ሃገራት ሰዎች...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል በዚህ ሳምንት ከ27 በላይ የሚሆኑ ‘ሰላማዊ ሰዎች’ “በመንግሥት ኃይሎች” መገደላቸው ተነገረ
     በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “የመንግሥት ኃይሎች” ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።የደብረሲና ከተማጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19፤ 2016 ዓ/ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን፤ በጥቃቶቹም ከ27 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር...
    June-29 - 2024 | More »
  • AMHARA MASSACRE: A GRIM REMINDER OF ETHIOPIA’S FRAGILE PEACE
     Mariam SenbetBeneath the rich history of Ethiopia lies a disturbing trend of violence that has disrupted the tranquility of its ancient monasteries and the well-being of its inhabitants. On February 22, 2024, a brutal assault resulted in the deaths of four monks within the sacred confines of...
    June-23 - 2024 | More »
  • More details emerging about ethnic Amhara Generals led public meeting in Addis
     On Friday, the Ethiopian Defense Force shared a brief update on its social media page about the meeting that the Deputy Chief of Staff, Abebaw Tadesse,  Defense Operations Manager, General  General Belay Seyoum, and Federal Police Deputy Commissioner, Zelalem Mengiste had with...
    June-23 - 2024 | More »
  • Dr. Fisseha Eshetu’s Claims Under Scrutiny: A Closer Look
     Dr. Fisseha EshetuBy Taye HaileDr. Fisseha Eshetu, the CEO of Purpose Black, has recently made headlines by claiming that he fled Ethiopia out of fear of arrest by the government. He alleges that government agents threatened him and accused him of supporting the group known as Fano. However,...
    June-23 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል ሁለት የጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “በመንግሥት ኃይሎች” ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ
     Bahir Darበአማራ ክልል ምዕራብ እና ምሥራቅ ጎጃም ዞኖች ባለፈው ሳምንት በቀናት ልዩነት ውስጥ ተፈጽሟል በተባሉ ጥቃቶች ከ20 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።ጥቃቶቹ ባለፈው ሳምንት ሰኔ 7 እና 9 ቀራኒዮ እና ጂጋ በተባሉ ከተሞች እንደተፈጸሙ የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ሁለቱም ጥቃቶች የመንግሥት ኃይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ካደረጉ በኋላ ስለመፈጸማቸው ገልጸዋል።እሁድ ሰኔ 9 በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህና...
    June-18 - 2024 | More »
  • ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ
     ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ያቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞች ከእስር ተፈቱ። ዛሬ እና ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ፣ ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው። ሶስቱ ጋዜጠኞች የፌደራል ፖሊስ “ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ በእስር እንዲቆዩ” ማድረጉን በመጥቀስ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት ነበር።...
    June-18 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time