Sunday, May 20, 2018

ጤፍንና ገበሬውን ከኢትዮጵያ የማጥፋት ዘመቻ

ጤፍንና ገበሬውን ከኢትዮጵያ የማጥፋት ዘመቻ?!
ውድ ኢትዮጵያውያን ይህንን ጽሁፍ በትእግስት እንድታነቡትና ሁኔታውን በውል እንድትመረመሩት አሳስባለሁ::
ኢትዮጵያ በግብርና ምርት ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ብትደርስ የሚጠላ ዜጋ የለም።ሆኖም አግባብ ባለውና የተፈጥሮ ሚዛንን በጠበቀ መንገድ እንጂ፤ እንዲሁ በምእራባውያን ፍላጎትና ግፊት ምንነቱ ባልታወቀ የኬሚካል ውህድ በመጣ ዘር መሆን የለበትም።በተመረዘ ምርት ከመጥገብ በጤና መራብ ይሻላልና።
ሰሞኑን በሳይንስና በቴክኖለጂ ሚንስቴር በኩል አንድ የምስራች የመሰለ አስደንጋጭ ዜና ይፋ ሆኖዋል።
ከዜናው እንጀምር።
"የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር አንድ ጊዜ ተዘርተው ለ10 እና ለ 20 አመታት በውሀ ብቻ ምርት መስጠት የሚችሉ የጤፍ እና የማሽላ ዝርያዎች በምርምር መገኘታቸውን አስታወቀ።
የተገኘው የጤፍ ዝርያ አንድ ጊዜ ከተዘራ በኋላ ለ10 አመት የማይሞት እና በየሶስት ወሩ ውሀ ብቻ ካገኘ ምርት መስጠት የሚችል ነው ተብሏል።
አዲሱ የጤፍና የማሽላ ዝርያ አንድ ጊዜ ተዘርቶ ለ20 አመት ድጋሚ መዝራት ሳያስፈልግ በየሶስት ወሩ ምርት መስጠት ይችላል ነው የተባለው።
አሁን ላይም ዝርያዎቹን ለሃገሪቱ ገበሬዎች ለማከፋፈል የዘር ብዜት ስራ እየተሰራ ሲሆን፥ ዝርያዎቹ በ2011 ዓ.ም የምርት ዘመን ለገበሬው የሚከፋፈሉ ይሆናል።
በኢትዮጵያዊ ተመራማሪ የተገኙት እነዚህ ዝርያዎች የኢትዮጵያን የሰብል ልማት ታሪክ መቀየር እንደሚችሉ ታምኖባቸዋል።"ይላል ዜናው።
ልብ በሉ!ይህ ግኝት በኢትዮጵያዊ ተመራማሪ አማካኝነት ተገኘ ተባለ እንጅ የግኝቱ ባለቤት የትኛው ኢትዮጵያዊ እንደሆነ በግልጽ አይታወቅም።"በኢትዮጵያውያን አማካኝነት"የሚለውም የተለመደው የምእራባውያን ማምታቻ መሆኑን ከልምድ እናውቃለን::
በኢትዮጵያውያን አማካኝነት ወይም በሚንስቴር መስሪያ ቤቱ በኩል በተካሄደ ምርምር የተገኘ ቢሆን ኖሮ፤ ይህ አይነቱ ዘር ለኢትዮጵያውያን ገበሬዎች እንደማይሆንና እንደማይጠቅምም በግልጽ ይታወቅ ነበርና ቀድሞ ቅድመ ዝግጅት ይደረግበት ነበር::ምክንያቱም የኢትዮጵያ ገበሬ ለምሳሌ ጤፍ ሲዘራ ቅድመ ዝግጅቱን በሰኔ ወር አጠናቅቆ ሃምሌ ላይ ዘርቶ ወቅቱን ጠብቆ አርሞና ጎልጉሎ ታህሳስ አካባቢ አጭዶና ከምሮ ከውቂያ በሁዋላ ምርቱን ይሰበስባል። ምርቱን ከሰበሰበ በሁዋላ ቃርሚያውን ለከብቱ ያበላል፤ጭዱንም እንደዚያው።
ከዚያ በሁዋላ ያ መሬት እንደገና ለአቅመ ጤፍ መዝሪያ ለመድረስ የራሱ የጊዜና የአየር ንብረት ሁኔታ ይፈልጋል።ይህ አይነቱ የጊዜና የአየር ንብረት ሁኔታ ደግሞ ከአዲሱ ግኝት ጋር ይጋጫል።በአዲሱ የዘር ግኝት መሰረት ዘሩ አንዴ ተዘርቶ ውሃ በማጠጣት ብቻ በየሶስት ወሩ ምርት ይሰጣል ከተባለ፤ የአረምና የጉልጉሎ ጉዳይ በየትኛው የጊዜ ልኬት ይከናወናል?አዱሱ ዘር ከተዘራ አረምም ጉልጉሎም የለም ከተባለ እንዲህ አይነት ምርት የጤፍ አለመሆኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል::ጤፍ በሃምሌ ይዘራል ሲባልኮ ሃምሌ ክረምት ስለሆነና ጤፍም ውሃ ስለሚፈልግ በዚያ ወቅት በመዘራቱ ምክንያት ውሃ እንደልብ ስለሚያገኝ ይስማማዋል ማለት አይደለም::ውሃ ብቻ ሳይሆን ከጸሃይ ብርሃንና ከደመና ጋር የተያያዘ የራሱ ፍላጎትና ጸባይ አለው::ከመሬት ጋርም እንዲሁ::ባጭሩ ጤፍ ውሃ ብቻ ስላገኘ ምርት የሚሰጥ ሰብል አይደለም።እንደዚያ ቢሆን ኖሮ በየትኛውም አካባቢና አገር ወይም በማንኛውም አይነት ውሃ ጠገብ የመሬት አይነት መብቀልና ምርት መስጠት ይችል ነበር::
ይህ ብቻ አይደለም አንድ የኢትዮጵያ ገበሬ ውሃ እንደ ልቡ አገኘ ብለን እናስብና በአዱሱ ግኝት አማካኝነት በየሶስት ወሩ ምርት ማግኘት ቻለ ብንል እንኩዋ፤ምርቱ ታጭዶ ከተከመረ በሁዋላ ራሱን በቻለ የጊዜ ልኬት መሰረት በጸሃይ ብርሃን መድረቅ አለበት::ለውቂያ ለመድረስ የግድ የታህሳስ አካባቢን የጸሃይ ብርሃን ይፈልጋል።ጤፍን ካጨዱ በሁዋላ ከጊዜው ቀደም ብሎ ወይም አሳልፎ መውቃት አይቻልም።በህዳር የታጨደን ጤፍ በጣም ቢዚ ነኝና ወደ መጋቢት ወይም ወደ ግንቦት አካባቢ እወቃዋለሁ የሚባልበት አካሄድ የለም::ወይም ጤፍን በመስኖ አማካኝነት ባሻን ጊዜ ዘርተን ባሻን ጊዜ ወቅተን የምናመርተው ምርት አይደለም።
የኢትዮጵያ ገበሬ የተፈጥሮን ሚዛን ጠብቆ ለብዙ ሺ ዓመታት ሲያመርተውና ሲመገበው ብሎም ሌላውን ሲመግብበት የኖረው የኢትዮጵያ ጤፍ በአይነቱም በአፈጣጠሩም በጸባዩም በይዘቱም በአየርና በመሬት ምርጫውም ሆነ በአመራረት ሂደቱ ከሌሎች ሰብሎች ፍጹም የተለየ ሰብል ነው::ጤፍ እንኩዋን በየሶስት ወሩ በአመት ሁለት ጊዜ ሊያመርቱት የማይችሉት ለየት ያለ ሰብል ነው።ሆኖም ዘመኑ የቴክሌጂ ነውና ተቻለ!ሊሉን ይችላሉ።ይህ ከተቻለ፤የተቻለበት ምክንያት የውስጥ ይዘቱ ወይም የጤፉ ፍሬ /ኢንግሪዲየንት/ የጤፍ ሳይሆን መልኩና ዘሩ ጤፍ መስሎ፤ነገር ግን ሌላ መርዛማ ኬሚካል ብቻ ነው ሊሆን የሚችለው።ወይም ከጤፍ የሚገኘውን ነገር ያላካተተ ሌላ ባእድ ነገር!
ይህ በትክክል የምእራባውያን ሴራ ለመሆኑ ብዙ ማስረጃ መደርደር ይቻላል::ባጭሩ ግን ጤፍ በባህሪው በየሶስት ወሩ ሊደርስ የሚችል ሰብል ካለመሆኑም በላይ ውሃ ስላገኘ ብቻ የሚመረት ሰብልም አይደለም!በዚህ መሰረት ይህን አዲሱን የጤፍ ግኝት በመዝራት የሚቆጠበው ምንድነው?ስንል ምላሹ ለዘር የሚሆነውን ሰብል ብቻ የሚል ይሆናል!ይህ ደግሞ ትርፍ አይባልም።ምክንያቱም በአንድ ሄክታር ላይ/አንድ ስቴዲየም በሚያክል መሬት ላይ/ ጤፍ ለማምረት የሚዘራው ዘር 20 ወይም 30 ኪሎ ግራም ጤፍ ብቻ በቂ ነውና።
ይህን ለመቆጠብና ገበሬውን ለማገዝ ከተባለ ደግሞ አስቂኝ እገዛ ይባላል!ገበሬውን ለማገዝ ከተፈለገ ከፍተኛውን የማዳበሪያ እዳ መቀነስ ወይም በነጻ መስጠት ያልቻለ ሴክተር ይህን ለገበሬው ጥቅም ስል ያደረኩት ነው ሊል አይችልም!ይህ ብቻ አይደለም።ገበሬው ይህን ዘር ዘርቶ ለ 10 እና ለ 20 ዓመታት ሳይዘራ ቁጭ አለ ማለት፤ ብዙ ነገር ማለት መሆኑ እንዳለ ሆኖ፤ያ መሬት ለሌላ ግልጋሎት እንኩዋ መዋል አይችልም ማለት ነው።የጤፍ መሬት ደግሞ ዘንድሮ ጤፍ ቀጥሎ ሌላ እየተዘራበት የሚብላላ የመሬት አይነት ነው።ጤፉ ታጭዶ ቃርሚያውን ከብቶች ሲመገቡት እንኩዋ ከምግብነት ባለፈ መሬቱ በከብቶች እንዲረገጥና መሬቱም እንዲናፈስ እንዲፍታታ የሚያደርጉበት ዘዴ ነው።የጤፍ መዝሪያ ወቅት ከመድረሱ በፊት ማሽላም ምንም እየተዘራበት የሚቆይ መሬት ነው።ገበሬው በእያንዳንዱዋ እለት የሚፈጽማት ተግባር ከተፈጥሮ ሚዛንና ከአየር ጸባይ ብሎም ከሌሎች ከወቅት ጋር ከተቆራኙ፤ ያለ ፊዚክስ ቀመር ፍሰታቸውን ጠብቀው ከሚተካኩ ከወቅት ክፍልፋዮች ጋር ራሱን አስማምቶና አዋህዶ የሚኖር ሊቅ ነው።ገና ለገና ምንም ምርጫ የሌለውና በማዳበሪያ እዳ እስረኛ የሆነ ማሃይም ነው ተብሎ የባእዳን ፍላጎት በግፍ ሊጫንበት አይገባም።ስለዚህ እንዲህ ያለውን ነገር የአገር በቀል ተመራማሪ ሊቀምረውና በኢትዮጵያ መሬት ላይ በኢትዮጵያዊ ገበሬዎች አማካኝነት ተግባራዊ ሊያደርገው አይደፍርም አይሞክርም ነበር።ነገር ግን ፍላጎቱና ግፊቱ ከምእራባውያን ሆነና ያለምንም የግንዛቤ ማስባጫ ትምህርትና ያለአንዳች ማብራሪያ በቀጣዩ ዓመት ለገበሬዎች ይከፋፈላል ተባለ።ይህንን አካሃድ አንድ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን መላው ኢትዮጵያዊ ነገሩ እስኪገባው ድረስ ሊቃወም፣ አስረዱን ሊልና፤ ሊጠይቅ ይገባል።ለገበሬውና ለሴክተር መስሪያ ቤቱ ብቻ የሚተው ጉዳይም አይደለም!
ለመሆኑ የትና እንዴት፤መቸና በምን መልኩ፤ በየትኛው ቤተ ሙከራና በየትኛው ክልል በሚገኝ መሬት ላይ ተሞከረ?ተሞክሮ ውጤታማ የሆነበት የምርምር ጣቢያ የት የሚገኝ ነው?ስለዚህ ጉዳይስ ሴክተር መስሪያ ቤቱ ለህዝቡ ጅምሩንና ሂደቱን የገለጸው መቸ ነው?ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል።ሚንስቴር መ/ቤቱ በዚህ ጉዳይ ላይ እየተመራመረ እንደሆነ/እንደነበረ/
በምንም አይነት መንገድና ሁኔታ ፍንጭ የሰጠበት ጊዜ የለም።ለዚህ ነው የኢትዮጵያውያን ግኝት ሊሆን አይችልም!ብሎ በድፍረት እውነታውን ለመናገር የተደፈረው።ይህ በቀጥታ የምእራባውያን ሴራ ነው!
ይህ ነገር ተግባራዊ ሆነ ማለት ብዙ ጉዳቶች እንደሚኖሩት ለማንም ባይሰወርም፤ተግባራዊ ሆኖ ምርት ይስጥም አይስጥም ፣የኢትዮጵያ ጤፍ አብቃይ መሬቶች በሙሉ ከ 10 ዓመት በሁዋላ ሙሉ በሙሉ ይመክናሉ!ጤፍም ብቻ ሳይሆን፤ማንኛውንም አይነት ዘር ሊቀበሉ የማይችሉ በድን መሬቶች እንደሚሆኑ ከወዲሁ ግልጽ መሆን አለበት!ከ 10 ዓመት በሁዋላ የኢትዮጵያ ገበሬዎች ሴክተር መ/ቤቱን ማለትም ምእራባውያኑን፤"10 ዓመት ሞልቶናልና ዘሩን ድጋሚ ስጡን"ሲሉ የሚያገኙት ምላሽ ምን ሊሆን እንደሚችልም ለአስተዋይ ኢትዮጵያውያን አይሰወርም።ስለዚህ ከወዲሁ ሊታሰብበት ይገባል እላለሁ!
Daniel Tomas 

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopian Health Professionals Association Urges Govt to Promptly Respond to Health Workers' Demands Amid Pre-Strike Demonstrations
     Dagmawi Melnilik Hospital, which was later upgraded to a referral hospital, is the nation’s first hospital, built in 1909.Addis Standard (Addis Ababa)As health professionals across Ethiopia stage pre-strike demonstrations demanding improved salaries, benefits, and working conditions, the...
    May-13 - 2025 | More »
  • Commentary: Why Ethiopian university lecturers' strike failed: A cautionary tale for health professionals
     The moment of release of the detained teachers’ coordinators, greeted by fellow teachers awaiting their return. Photo: Provided by the writerIn 2022, Ethiopian university lecturers launched a year-long social media campaign  and subsequent threat for indefinite...
    May-13 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-08 - 2025 | More »
  • ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ
     የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ...
    May-08 - 2025 | More »
  • በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት
     ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ...
    May-05 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-05 - 2025 | More »
  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው  ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time