Tuesday, October 10, 2017

የኦሮሚያና የሶማሌ ግጭት ሙሉ በሙሉ እንዳልቆመ መንግሥት አስታወቀ

በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች መካከል ከወር በፊት ተቀስቅሶ የነበረው ግጭት እስካሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ እንዳልቆመ መንግሥት አስታወቀ፡፡
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትር ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ዓርብ መስከረም 26 ቀን 2010 ዓ.ም. ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በሁለቱ ክልሎች መካከል የከፋ ግጭት ባይኖርም በየቀኑ አልፎ አልፎ ግጭት መከሰቱ ቀጥሏል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በኩል እስካሁን ድረስ እየሞቱና እየተፈናቀሉ ያሉ ሰዎች በየቀኑ ሪፖርት እየተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ድረስም ጉዳቶች እንዳሉ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡ ይህ የሚያመለክተው ደግሞ የታጠቀ ኃይል ሰርጎ እየገባና ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ነው ብለዋል፡፡
በሁለቱ ክልሎች መካከል ተቀስቅሶ የነበረውን ግጭት በተመለከተ ለመገምገምና አዳዲስ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ሲባል ባለፈው ሳምንት አጋማሽ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሁለቱን ክልሎች አመራሮች አግኝተው እንዳነጋገሯቸው ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
በዚህ ውይይት ላይ ከኦሮሚያ ክልል የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከሶማሌ ክልል ደግሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሐመድና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ግጭቱ የዜጎችን በሕይወት የመኖርና ንብረት የማፍራት መብቶች የጣሰ እንደሆነ መግለጻቸውን ጠቁመዋል፡፡ የኦሮሞና የሶማሌ ሕዝቦችን የማይወክሉ ኃይሎች ባደረሱት ግጭት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሕይወት መጥፋት ተገቢ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት ማስተላለፋቸውንም ተናግረዋል፡፡
ጉዳት ከደረሰባቸው ዜጎች ጋር በተያያዘ የኦሮሚያ ክልል ባቀረበው ሪፖርት መሠረት ከ75 ሺሕ በላይ የሚሆኑ የኦሮሚያ ተወላጆች ከሶማሌ ክልል መፈናቀላቸውን፣ ከኦሮሚያ ክልል ግን 392 የሶማሌ ተወላጆች መፈናቀላቸውን እንዳስታወቀ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ከአወዳይ አካባቢ ምሥራቅ ሐረርጌ የተፈናቀሉና ወደ ጅግጅጋ የሄዱ እንዳሉም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ  ኦሮሞዎች የሶማሌ ሕዝብ እንዳላፈናቀላቸው፣ አንዳንዶቹ በተለያዩ አካላት ተገፍተው፣ ሌሎቹ ደግሞ በአመራሩና በፀጥታ አካሉ ላይ እምነት ስላልነበራቸው ከሶማሌ ክልል መፈናቀላቸውን እንደገለጹም ጠቅሰዋል፡፡
‹‹ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉት ምናልባት 400 ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ በኦሮሚያ በኩል የተገለጸው ይህ ነው፡፡ እንዲያውም አወዳይ አካባቢ የደረሰውን ጥቃት የከፋ እንዳይሆን ያደረገው የኦሮሞ ሕዝብ እነዚህን ተፈናቃዮች ደብቋቸው ወደ ሐረር እንዲሄዱ በማድረጉ ነው፤›› ብለዋል፡፡
በሕዝቡ መሀል ችግር ከሌለ ይህ ግጭት ለምንድነው የተከሰተው ለሚባለው አመራሩ ራሱን እንዲፈትሽ የሚያስገድድ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጻቸውንም ተናግረዋል፡፡
‹‹በዚህ ግጭት እስካሁን ድረስ ምን ያህል ሰው እንደሞተ ሁለቱም ክልሎች የሚገልጹት እንዳለ ሆኖ፣ በአሁኑ ወቅት እየተጠና ስለሆነ ወደፊት ለሕዝቡ ይፋ ይሆናል፤›› ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንም በግጭቱ ምክንያት የደረሰውን ጉዳትና የሞተውን የሰው ቁጥር ለማወቅ በአሁኑ ወቅት እያጠና መሆኑን ጠቁመው፣ ‹‹በቅርብ ጊዜ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርት ያቀርባል፤›› ሲሉ ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅትም ከሁለቱ ክልሎች ወንጀል የፈጸሙትንና ለግጭቱ መንስዔ የሆኑትን የፌዴራል ፖሊስ እያጣራና በቁጥጥር ሥር እያዋለ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ግጭቱን ለማስቆም ሲባልም የሁለቱ ክልሎች የፀጥታ አካላት ከአዋሳኝ አካባቢዎች እንዲርቁ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም አቅጣጫ መስጠታቸውን አስታውሰዋል፡፡ በዚህ መሠረትም የሁለቱም ክልሎች ሚሊሻዎች ከወሰን አካባቢ አምስት ኪሎ ሜትር እንዲርቁ፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እየተባለ የሚጠራው ፖሊስና የኦሮሚያ ክልል ፖሊስም ከአዋሳኝ አካባቢዎች ከአሥር እስከ 20 ኪሎ ሜትሮች መራቅ እንዳለበት አቅጣጫ መቀመጡን አስረድተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት መንግሥት በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ ታጣቂዎችን ትጥቅ እያስፈታ ነው እየተባለ በተለያዩ ሚዲያዎች እየተገለጸ እንደሆነ ያስታወሱት ሚኒስትሩ፣ ይህ ውሸት እንደሆነና የተከለከለውን ዞን ጥሰው የሚገቡ አካላት በቁጥጥር ሥር የማዋል ሥራ ግን እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሁለቱ ክልሎች መካከል በተፈጠረው ግጭት የወጪ ንግድ መስተጓጎል እያስከተለ እንደሆነ መንግሥት መገምገሙን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ በምሥራቅ በኩል ጫትና ሌሎች ምርቶች እንዲቆሙና እንዲቃጠሉ በመደረጉ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ ይህ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ በፊት ያስቀመጡትን አቅጣጫና መመርያ የጣሰ መሆኑ ታውቆ ለወደፊቱ እንዲስተካከል አቅጣጫ መስጠታቸውን አስረድተዋል፡፡
ለጫትና ለሌሎች ሸቀጣ ሸቀጦች መስተጓጎል ምክንያቱ ደግሞ በሁለቱ ክልሎች ውስጥ ያለው ኬላ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁለቱም ክልሎች በገቢና በወጪ የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ኬላ ማቆም እንደሌለባቸው፣ ወደፊት በፌዴራል መንግሥት ሥር ሆነው መሥራት እንደሚገባቸው መናገራቸውንም ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከሁለቱም ክልሎች የተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን በተመለከተም በጊዜያዊነት የሚያስፈልጋቸው ድጋፍ በአፋጣኝ እንዲደረግላቸው፣ የተጎዱት ንብረታቸው የሚመለስበትና ለወደመባቸው ደግሞ ካሳ የሚያገኙበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማሳሰባቸውን ተናግረዋል፡፡
የሶማሌ ክልል መንግሥትና የአገር ሽማግሌዎች ባለፈው ሳምንት ያወጡትን መግለጫ በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አይተው እንዳዘኑና እንደዚህ ዓይነት መግለጫ ለወደፊት መውጣት እንደሌለበት ጥብቅ ማሳሰቢያ መስጠታቸውን አስረድተዋል፡፡
የሶማሌ ክልል መንግሥትና የአገር ሽማግሌዎች ማክሰኞ መስከረም 23 ቀን 2010 ዓ.ም. የጋራ መግለጫ ያወጡ ሲሆን፣ መግለጫው የሶማሌ ሕዝብ የቀድሞውን የደርግ ሥርዓት ለማስወገድ በተደረገው ትግል ሕዝቡ መስዋዕትነት እንደከፈለ አስታውሷል፡፡ መግለጫው በሁለቱ ክልሎች መካከል ለተቀሰቀሰው ግጭት ዋነኛ ተጠያቂ የኦሮሚያ ክልልን አድርጓል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ግን በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopian Health Professionals Association Urges Govt to Promptly Respond to Health Workers' Demands Amid Pre-Strike Demonstrations
     Dagmawi Melnilik Hospital, which was later upgraded to a referral hospital, is the nation’s first hospital, built in 1909.Addis Standard (Addis Ababa)As health professionals across Ethiopia stage pre-strike demonstrations demanding improved salaries, benefits, and working conditions, the...
    May-13 - 2025 | More »
  • Commentary: Why Ethiopian university lecturers' strike failed: A cautionary tale for health professionals
     The moment of release of the detained teachers’ coordinators, greeted by fellow teachers awaiting their return. Photo: Provided by the writerIn 2022, Ethiopian university lecturers launched a year-long social media campaign  and subsequent threat for indefinite...
    May-13 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-08 - 2025 | More »
  • ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ
     የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ...
    May-08 - 2025 | More »
  • በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት
     ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ...
    May-05 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-05 - 2025 | More »
  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው  ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time