Saturday, August 4, 2018

በጂግጂጋና ሌሎች የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በፍጥነት ሊገታ ይገባል:- ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር

በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል በጂግጂጋ ከተማ ሌሎች አንዳንድ የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና በፍጥነት ሊገታ እና ሊታረም የሚገባው መሆኑን የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

መከላከያ ሠራዊቱ ከሌሎች የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመሆን የተከሰተውን ሁከት በቅርበት ሲከታተልና ሁኔታውን ለመቆጣጠርና ህብረተሰቡን ለማረጋጋት ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጅ እንደሚወስድ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል፡፡

የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ ከመንግስት ኮሙኒከረሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ደርሶናል እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

አገራችን ኢትዮጵያ የህዝቦቿን ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ በለውጥ ሂደት ውስጥ እንደሆነች ይታወቃል።
ለውጡም መላ የኢትየጵያ ህዝቦችን ባሳተፈ እና ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል።
እየተካሄደ ካለው የለውጥ እንቅስቃሴም መላው የአገራችን ህዝባችን ተጠቃሚ በመሆናቸው ተሳትፏቸውን በማጠናከር ላይ ይገኛሉ።

ሆኖም በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች አልፎ አልፎ የብጥብጥና የሁከት ድርጊቶች ይስተዋላሉ።
እነዚህ ህገወጥ ድርጊቶች በሚስተዋሉባቸው አካባቢዎች የጸጥታ ሃይሉ ከህዝቡ ጋር ሆኖ የማረጋጋት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል።

በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል በጂግጂጋ ከተማ የተከሰተው ብጥብጥ፣ ቀጥሎም ወደ ሌሎች አንዳንድ የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና በፍጥነት ሊገታ እና ሊታረም የሚገባው ድርጊት ነው።

የአገር መከላከያ ሠራዊታችን ከሌሎች የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመሆን የተከሰተውን ሁከት በቅርበት ሲከታተልና ሁኔታውን ለመቆጣጠርና ህብረተሰቡን ለማረጋጋት ጥረት እያደረገ የነበረ ቢሆንም ብጥብጡ በተፈለገው ፍጥነት ሊቆም አልቻለም።

በመሆኑም በክልሉ የሚኖሩ ህዝቦቻችን ደህንነት እና ሰላም አደጋ ውስጥ እየገባ ያለበት ሁኔታ በመፈጠሩ የመከላከያ ሃይላችን ሁከትና ብጥብጡን በዝምታ የማይመለከት መሆኑንና ችግሩንም ለመቅረፍ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በጥብቅ ማሳሰቡን የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።

የአብዲ ዒሌ እብደት

የአብዲ ዒሌ እብደት

ሰበር ዜናውን ኢሳት ላይ እንዳየሁ ነው ወደዚህ የመጣሁት። የሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጂጂጋ ሙሉ በሙሉ በመከላከያ ሰራዊት እጅ ገብታለች። የመንግስት መስሪያ ቤቶችና ዋና ዋና የከተማዋ ክፍሎች በፌደራሉ መንግስት ቁጥጥር ስር ገብተው ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገላቸው ነው። ጂጂጋ ያለው ነገር ግልጽ አይደለም።
አብዲ ዒሌ እያበደ ነው። እንደሰማሁት የሶማሌ ክልልን ከእናት ሀገሩ እገነጥላለሁ ብሎ ሊያውጅ አፉን በልቶታል። ካቢኔውን ለዚሁ ጉዳይ ትላንት ምሽት እንደሰበሰበው መረጃውን አግኝቼአለሁ። የፌደራል መንግስቱ ቁንጥጫ ሲጠነክርበትና ህዝቡም አይንህን ለአፈር ሲለው የፈረደበትን ''እንገነጠላለን'' ቀረርቶ እያሰማ ነው። የጡት አባቱ ጄነራል ኳርተር ያስጠናው አንድ ነገር ቢኖር ይህቺው አንቀጽ 39 ናት። አርጩሜ በቀመሰ ቁጥር የሚመዛት የተለመደች ዲስኩር። ለአብዲ ዒሌ ህግ ከቃል ያለፈ ትርጉም የለውም። አንቀጽ 39ኝን እየጠቀሰ ማስፈራራት ለዘመናት የተጠቀመው ስትራቴጂ ነው። ዘንድሮም አልቀቀም።
አብዲ ዒሌ አፍንጫው ስር የሚያሸተው ውድቀቱ ደም እንዳስከረው ውሻ እያቅበዘበዘው ነው። የሶማሌ ኢትዮጵያውያንን ሰብዓዊ ጋሻ በማድረግ የአብይን አስተዳደር ለማስጨነቅ መዘጋጀቱን ነው መረጃዎች የሚያመለክቱት። ትላንት ምሽት የሰበሰበው ካቢኔው ምን ውሳኔ እንዳስተላለፈ ባይታወቅም የአብዲ ዒሊን ቅዥት ይቀበላል ተብሎ የሚገመት አይደለም። አዝማሚያው ያላማራቸው ዶ/ር አብይ ዛሬ መከላከያ ሰራዊቱ ጂጂጋን እንዲይዝ አድርገዋል::
አዎን!ሶማሌ ክልል ተቃውሞው አገርሽቷል። ህዝቡ ቆርጧል። የአብዲ ዒሌን አስተዳደር ፈንቅሎ ለመጣል የመጨረሻውን ምዕራፍ ተጥግቷል። አብዲ ዒሌ ህወሀት ላይ ጣቱን ከቀሰረና የቀድሞውን ደህንነት ሃላፊ ጌታቸው አሰፋ ላይ ሃጢያቱን ከደፈደፈ በኋላም ከተጣባው የመግደል አመል አልተላቀቀም። ጄል ኦጋዴንን ዘጋሁ በሚል ዕለም ዓቀፉን ማህብረሰብ ለማደናገር የሄደበት ርቀት ከእዚያ ከጂጂጋ የሚያስወጣው አልነበረም።
አብዲ ዒሌ ለዶ/ር አብይ ብርቱ ፈተና መሆኑ ሲጠበቅ ነበር:። ህወሀት ይሄን ሰው በመጠቀም የጥፋት ሚናውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት ሲገለጽ ቆይቷል። በእርግጥም ያኮረፈውና መቀሌ የመሸገው የህወሀት ቡድን እጅና እግሩ ቢቆረጥም ምላስና ገንዘቡ ግን አልተነካም። ለውጡን ለመቀልበስ እንቅልፍ አጥተው ማደር ከጀመሩ ሰንበትበት ብለዋል። ከሰሜን እስከደቡብ: በምስራቅም በምዕራብ እሳት በመጫር ኢትዮጵያን የቀውስ ሀገር በማድረግ የዶ/ር አብይ መንግስት ያልተረጋጋ: ሰላም የራቀው አድርጎ ማሳየት የህወሀት የሽንፈት ፓለቲካ መገለጫ ሆኗል። በሰሜን ጎንደርም የቅማንትን ካርድ በመሳብ አደገኛ ጨዋታ ጀምራል:: በረከት ስምዖን በሰው ደም እድሜውን ለማርዘም ጭልጋ እየተመላለሰ መሆኑ ተስምቷል። ህወሀት በአንዳንድ የሀገሪቱ አከባቢዎችም ተመሳሳይ ግጭት በመፍጠር ላይ ተጠምዷል።
የአብይ አስተዳደር ከያቅጣጫው ጫና እየበረታ መጥቶበታል። እርምጃ እንዲወስዱ እየተጠየቀ ነው።ከኢንጅነር ስመኘው ግድያ በሃላ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ እየገፋ የመጣውና ህግን እንዲያስከብሩ እየተደረገ ያለው ግፊት ተጠናክሯል። አፋጣኝ ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች በደህንነት መስሪያ ቤቱ መዝገብ ቤት ተከማችተው እንደሚገኙም ይነገራል። በሀገር ላይ ከፍተኛ በደልና ወንጀል የሰሩ በተለይ የህወሀት መሪዎችን ለማሰር የሚያስችል በቂ መረጃና ማስረጃ ተጠናቅሮ ማለቁ ተሰምቷል። እነዚህ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ፊርማ የሚጠብቁ ትልልቅ ጉዳዮች በቶሎ ተግባራዊ ካልተደረጉ በእሳቸው ላይ መልሶ ከመባረቅ አንስቶ ሀገሪቱን ወደ ትርምስ እንዳይከታት ስጋቱ ከአፍንጫ በር ስር የሚሰነፍጥ ሆኗል።
በእርግጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣናቸውን ማረጋጋቱና የበለጠ ቀውስን ከሚፈጥሩ ውሳኔዎች ለጊዜው መራቃቸውን የሚደግፉ ሰዎች አሉ። መቀሌ መሽጎ የሚያለቃቅሰው የህወሀቱ ቡድን እጅ ባልሰጠበትና የመረበሽ አቅሙ ባልሟሸሸበት: አሁንም ከጥፋት መንገዱ ላይ የቆመው የትላንቱ መንግስት የዛሬው ሽፍታ ቡድን እያለ ከበድ ያሉ እርምጃዎችን ባይወስዱ ይመረጣል የሚሉ በርክተዋል። ህወሀት ከቤተመንግስት ተባረረ እንጂ አልሞተም። ከእንግዲህ ቤተመንግስት የመግባት እድሉ የማይታሰብ ቢሆንም የጥፋት ሃይል ሆኖ ለጥቂት ጊዜያት መቀጠል የሚያስችል አቅም እንዳለው ይታወቃል።
ህወሀት አረናዎችን ከጎኑ በማሰለፍ መቀሌ ላይ እየመከረ ነው። ብዙ ሚስጢራዊ ስብሰባዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። ወይ እንከባበር አልያም እንበታተን የሚል መፈክር ከመቀሌ ክፍ ብሎ ይታያል። ህወሀቶች እርምጃው ወደ እነሱ ከመምጣቱ በፊት ሌላው ጋ ቀውስ መፍጠርን እንደስትራቴጂ እየተጠቀሙ ነው። ጂጂጋ ጥሩ ቤንዚን ናት። ትንሽ እሳት ካየች ትቀጣጠላለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጂጂጋ ላይ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ ከሚመጣው አደጋ አንጻር ተገቢ ይመስላል። አብዲ ዒሌ የመጨረሻ ጥይቱን ሊተኩስ መዘጋጀቱን የሰሙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ቀድመው መከላከያ ሰራዊታቸውን አስገብተዋል። ምንም እንኳን በህገመንግስቱ የመገንጠል መብት ውስብስብና ዓመታትን በሚፈጅ ሂደት የሚከናወን ቢሆንም ህዝቡን ውዥንብር ውስጥ ለመክተትና ሰላም ለማደፍረስ በቂ ሰበብ መሆኑ አይቀርም። የህወሀት ስትራቴጂ ሰላም ማሳጣት ነው። መንግስትን መረበሽ ነው። ለውጡን ማደናቀፍ ነው። ለዚህ እንደአብዲ ዒሌ ጥሩ መሳሪያ ቢፈለግ አይገኝም።
እናም ጂጂጋ ውጥረት ውስጥ ናት። መረጃዎች በየሰዓቱ እየተቀያየሩ ነው። ሰሞኑን አብዲ ዒሌ በከፈተው መጠነ ሰፊ የማጥቃት ዘመቻ ምክንያት በ10ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ወደ ጅቡቲ ሸሽተዋል። የአብዲ ዒሌ ጸሀይ እየጠለቀች ቢሆንም በቀላሉ እጅ አልሰጥም እያለ ነው። መቀሌ የመሸገው የህውሀት ቡድን በገንዘብና በፕሮፖጋንዳ ከአብዲ ዒሌ ጎን መሰለፉም ይነገራል። የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የዛሬው እርምጃ የአብዲ ዒሌን ፍጻሜ ያቃርበው ይሆን?
Mesay Mekonnen

Friday, August 3, 2018

ተስፋ ሰጭው የሳይንስ ትግበራ -የሮኬት ሙከራ

ተስፋ ሰጭው የሳይንስ ትግበራ፡፡

‹‹የማዕከሉ ሙከራዎች ኢትዮጵያ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ ለመድረስ ላሰበችው እቅድ አቅም ይሆናል።››
‹‹የተማሪዎችን ፈጠራ በእውቀት እና በገንዘብ የምንደግፍበት ወቅት ነው›› የባሕርዳር ሳይንስ ማበልፀግያ ማዕከል፡፡

ሳይንስ ለችግሮች መፍትሄ ለማምጣት የምንጥርበት የእውቀት እና ክህሎት መድረሻ ነው። የሁሉም ስኬታማ ሳይንስ መነሻው ችግር ፣ ትንንሽ ሙከራዎች እና የሚያድጉ ፍላጎቶች ናቸው።
በባሕርዳር ሳይንስ ማበልፀግያ ማዕከል ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች ሮኪቶችን ማምጠቅ የሚቻልበትን ሳይንሳዊ ትግበራ እየሰሩ ነው።
የ11ኛ ክፍል ተማሪዎቹ ናሆም ፈረጃ እና ኑር አህመድ አባይ በውሃ ሃይል እምቅታ እና በኬሜካል የሚመጥቁ ሮኪቶችን ሰርተዋል።
የተማሪዎቹ ግኝት ከሶስት ዓመታት በላይ የወሰደ ሳይንሳዊ ግኝት ነው የሚሉት የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋየ ሽፈራው ሳይንስን መተግበር እንደተጀመረ ማሳያ ነው ይላሉ።
ዶክተር ተስፋየ እውነታው ግን ተማሪዎቹ በውሃ እምቅታና በኬሜካል ሊያመጥቁ የሚችሉ ትግበራዎችን በግሃድ ማሳየት የሚችሉበት አቅም ፈጥረዋል።
የሚሰሩት ቁሳቁስ በአከባቢው ከሚገኙት በመሆኑ የሚወነጨፈው ሮኪት ለሃገራዊ ጥቅም የሚውል አይደለም። እንደነዚህ አይነት ሙከራዎችን ግን ከትንሽ እስከ ትልቅ ችግር ለመፍታት እንዲያስችል ወደ ምርት ለማስገባት እገዛዎች ያስፈልጉናል ብለዋል።
የተማሪዎችን ፈጠራ ጥቅም ላይ ለማዋል ተጨማሪ እውቀት ማበልፀግ እና በገንዘብ የምንደግፍበት ወቅት ላይ ደርሰናል። ኢትዮጵያ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ ለመድረስ ላሰበችው እቅድም አቅም የሚያጎለብቱ በመሆኑ ተማሪዎቹ የተሻለ ስልጠና እንዲያገኙ በገንዘብ እንዲደገፉ መስራት እንደሚያስፈልግ ዶክተር ተስፋየ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡-ግርማ ተጫነ






Sunday, July 29, 2018

የአቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ



የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።

የታላቁ ኅዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ስመኘው በቀለ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ። አዲስ አበባ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል በተካሔደው የቀብር ሥነ-ሥርዓት የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ፣ ምክትል ጠቅላይ ምኒስትር ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ሹማምንት ተገኝተዋል።  
ድንገተኛ ዜና ዕረፍታቸው ከተሰማ ጀምሮ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የተፈጠረው ሐዘን እና  ቁጭት አለመብረዱ በመስቀል አደባባይ በተካሔደው የሽኝት መርኃ-ግብር ላይ ታይቷል። በሽኝት መርኃ-ግብሩ ላይ ገዳዮቻቸው ለፍርድ ይቅረቡ የሚሉ በርካታ ድምፆች መሰማታቸውን የአይን ዕማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። አቶ ስመኘው ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም መስቀል አደባባይ አካባቢ በተሽከርካሪያቸው ውስጥ ሞተው መገኘታቸው ከተሰማ በኋላ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ሐዘን ተፈጥሯል። ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ የምኅንድስና ባለሙያው አቶ ስመኘው በቀለ የሞት "ዜና ልብ ይሰብራል" ሲሉ ተናግረዋል።
የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አቶ ዘይኑ ጀማል ስለ አሟሟታቸው "አመላካች መረጃዎች እና ማስረጃዎች" መገኘታቸውን የተናገሩ ሲሆን "በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሞተ፣ ለምን እንደሞተ የሚገልጹ መረጃዎችን ለኅብረተሰቡ" እናሳውቃለን ብለዋል።
የ53 አመቱ አቶ ስመኘው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሲቪል ምኅንድስና ያገኙ ሲሆን በግልገል ጊቤ 1 እና ግልገል ጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች መርተዋል። ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ በተባለው ቦታ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የታላቁ ኅዳሴ ግድብ እስከ ዕለተ-ሞታቸው በኃላፊነት ሲመሩ ቆይተዋል።
ከአባታቸው አቶ በቀለ አይናለም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘነቡ አብተው መስከረም 3 ቀን 1957 ዓ.ም. በቀድሞው ጎንደር ልፍለ ሀገር ጠዳ ወረዳ ልዩ ስሙ ማክሰኚት ከተባለ ተወለዱ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በእንፍራንዝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደሴ ቅዳሜ ገበያ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወልዲያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መከታተላቸውን በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተነበበው የሕይወት ታሪካቸው ይጠቁማል።

Thursday, July 26, 2018

Who killed Engineer Simegnew & why? (just asking)

Who killed Engineer Simegnew & why? (just asking)
State-owned Ethiopian Electric Power ( # EEP ) has failed to produce a detailed financial report for the last two years.
The problems are partly due to the weaknesses of a bloated and hierarchical utility company. Decision-making at EEP is sluggish and there are not enough empowered managers, according to individuals who work with the corporation. EEP executives are over-burdened and lack technical expertise. One consultant said even decisions to purchase cables now have to get board approval because of a lack of trust in the management. A donor representative said EEP has failed to produce a detailed financial report for the last two years. Such issues are typical of Ethiopia’s public sector, which is weakened by meager salaries, places a premium on political loyalty, and is partly an ethnic balancing act when it comes to senior appointments.
#Military_Power
Politics is also relevant at the top of an industry where veterans of the armed struggle exert considerable influence. EEP’s board is chaired by
#Debretsion_Gebremichael , a minister who was a leading engineer for the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) during the 17-year rebellion that ended with the Derg regime crumbling in 1991. The originally Leninist TPLF formed the core of the revamped military and founded the revolutionary ruling coalition that still dominates Ethiopian politics.
Debretsion oversees the # GERD, whose electro-mechanical works were contracted to a conglomerate run by military officers. Lacking the requisite experience, that group, the Metals and Engineering Corporation ( #METEC ), sub-contracted turbine construction to France’s Alstom and Germany’s Voith Hydro. While a foreign adviser says METEC’s role in the GERD has not caused problems, it has failed to deliver seperate sugar and fertilizer factories on time while pocketing substantial payments in advance. For years the ruling coalition has identified surging corruption as the primary domestic threat to realizing Meles’ development vision.
In an interview with The Reporter newspaper in March, Debretsion bullishly defended METEC’s role, arguing it helped stave off foreign pressure to downsize the GERD and was necessary to build domestic industrial capacity. He was also positive about the prospects for private investment in Ethiopian energy projects. But such views demonstrate the conundrums for Addis Ababa’s policy makers: despite the need for foreign capital, there are long-held suspicions from Marxist-influenced politicians about private profiteering; and the effort to rapidly boost energy production is sometimes at odds with aspirations to improve local engineering capabilities.
According to one energy consultant, these attitudes are a major obstacle to sustaining Ethiopia’s impressive momentum in the power sector, especially when it comes to facilitating the development of privately owned power plants. “There is still a question of whether at the highest level of the government they understand what an IPP is. It could have exploded with development if the right people were managing the economy,” the consultant said.
By William Davison

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time