Thursday, July 19, 2018
መንግሥት በዶላር ጉዳይ መግለጫ ሰጠ
Wednesday, July 11, 2018
በአሁኑ ወቅት የኦሮሞ ነፃ አውጪ ነኝ በሚል ስም የጦርነት አዋጅ እያወጀ ያለው አካል ፣ እያደረገ ያለው ነገር እንዲያስብበት እና ወደትክክለኛው መንገድ እንዲመለስ ኦቦ ለማ መገርሳ አስጠነቀቁ
በአሁኑ ወቅት የኦሮሞ ነፃ አውጪ ነኝ በሚል ስም የጦርነት አዋጅ እያወጀ ያለው አካል ፣ እያደረገ ያለው ነገር እንዲያስብበት እና ወደትክክለኛው መንገድ እንዲመለስ ኦቦ ለማ መገርሳ አስጠነቀቁ። የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦቦ ለማ መገርሳ የጦርነት አዋጅ ያወጀውን ቡድን ያስጠነቀቁት፣ ትናንት በኦሮሚያ ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር ነው። “ከዚህ በፊት ቀጥታ ሲዋጉን የነበሩ አካላት ዛሬ ስፓንሰር በመሆንና ገንዘባቸውን በመርጨት የክልሉት ፀጥታ ለማደፍረስ እንቅልፍ አጥተው እየሰሩ ይገኛሉ ያሉት አቅቶ ለማ፣ ከስፓንሰሮቹ የሚለገሳቸውን ገንዘብ በመቀበል የተሰጣቸውን ተልዕኮ ለማስፈፀም ዝግጁ የሆኑ በርካታ የእኛው ወንድሞችም በመከላችን ይገኛሉ” ብለዋል፡፡ “ለዚህ ህዝብ ሁላችንም እንሥራለት በሚል ውሳኔ ሁሉም ወደ ሀገር ተመልሶ በሀሳብ በመፋለም አንድ ላይ መስራት አለብን ብለን ጥሪ ከማድረግም በላይ ፣ ህዝባችንን አምነን ብዙዎቹን ከሰሩት ወንጀልም ነፃ እንዲሆኑ አደረግን “ ያሉት ር ዕሰ መስተዳድሩ፣ የፓለቲካ ታርጋ ተለጥፎባቸው በሰው ሀገር የተበተኑ ወገኖቻችን ተመልሰው ለሀገር እንዲሰሩ በራፉን በከፈትንበት ፣ ብዙዎች ጥሪዎን ተቀብለው እየገቡ ባለበት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን እየፈታን ባለንበት እና አጠቃላይ የፓለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ ባለበት ጊዜ ፣”አይ! የኦሮሞ ነፃነትን ለማስከበር ትክክለኛ የጦርነት መክፈቻው ጊዜ አሁን ነው” ተብሎ በኦሮሞ ህዝብ ስም የሚደረግ እንቅስቃሴ ትርጉሙ ምን እንደሆነ በግሌ አልገባኝ”ብለዋል። አቶ ለማ አክለውም፦”ለኦሮሞ ነፃነት ለማስከበር የሚያስቡ ከሆነ ፣እስከዛሬ ይሄን ሁሉ ዘመን የት ነበሩ?…ሲሉ ጠይቀዋል። . “ እነዚህ ወገኖች ከልጅ ፊት አባት ገድለው ሬሳውን አቃጥለዋል።ሬሳ በማቃጠል የህዝብ ነፃነት እንዴት መከበር እንደሚችል አላውቅም። ኦሮሞ-ኦሮሞን ነው እየገደለው ያለው።…በምዕራብ ኦሮሚያ እየሆነ ያለው ነገር ይሄ ነው፡፡” ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አክለዋል። “ቄሮ ለዓመታት በመሪነት ባደረገው ትግልና በከፈለው መስዋዕትነት አሁን እያየነው ያለነው ለውጥ እንዲመጣ እና ዛሬ የመጣውን ውጤት እንድንጎናፀፍ አድርጎል.” ያሉት ኦቦ ለማ መገርሳ፣ “ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በቄሮ ስም ለመነገድ የሚሞክሩ ወጣቶች እዚህም እዛም የመዝረፍና አንዳንድ አካባቢዎችን የማወክ አዝማሚያ እያሳዩ እንደሆነ አልሸሸጉም። “ቄሮዎች ግን ይሄ በታሪክ ማህደር ላይ የተከተበ የጀግንነትና ለህዝብ መስዋዕትነት የከፈሉት ደማቸው ባክኖ እንዲቀርባቸው ስለማይፈልጉ፣ አሁንም እነዚህን ቅጥረኞች አደብ በማስገዛት እና ወደመስመር በማስገባት ረገድ ትልቅ ምሳሌ የሚሆን ስራ በመስራ ላይ ይገኛሉ”ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ “ህዝባችንም እንደዛው እያደረገ ነው፡ብለዋል። ይህ ሕግን የማስከበርና ሰላምና መረጋጋትን የማረጋገጥ ተግባር በሁሉም አካባቢ ተጠናክሮና ተስፋፍቶ መተግበር እንዳለበትም አቶ ለማ አሣስበዋል፡፡ “በአሁኑ ወቅት በክልላችን መዋቅር ውስጥ እንደ ኦሮሚያ ፖሊስ ለህዝቡ ዋልታና መከታ የሆነ አካል አኔ በግሌ አላውቅም” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በዛ በጭንቀትና በመከራ እና አይዟችሁ የሚለን ባጣንበት ጊዜ ከጎናችን ቆሞ ደሙን እያዛራ እና ህይወቱን እየሰጠ ለዚህ ለዛሬው ቀን እንደንደርስ የሚችለውን ሁሉ ያደረገ የህዝብ አካል ነው”ብለዋል። አቶ ለማ አክለውም፦”የኦሮሚያ ፓሊሶች ለሚከፈላቸው ደሞዝ አየይደለም ፋቲኩን የለበሱት፡፡ እኔ እንደ ኦሮሚየ ፓሊስ በቁርጠኝነት ለህዝብ የቆመ አላውቅም።ቁርስ በልቶ ምሳ ሳይደግም ፀሀይና ንፋስ እየተፈራረቀበት መካራውን በማየት ከገዛ ስንቁ ለህዝቡ እየቀነሰ ሲሰቃይ የነበረ የህዝብ ወገን ነው።ለህዝባቸው ሲሉ ቤተሰባቸውን በትነው በየቆላውና በየድንበሩ በርካቶቹ ህይወታቸውን አጥተዋል። …. ታዲያ እንዴት ዛሬ በኦሮሚያ ፓሊስ ላይ ልክ እንደህዝብ ጠላት ቦንብ ይጣልበታል…? ይህ ፖሊስ እንዴት ዛሬም ይገደላል……?ምን ተፈልጎ ነውአሁን አንዳችን በሌላችን ላይ ቂም እንድናወጣ ጥሪ እየተደረገ ያለው?”ሲሉ በአጽንዖት ጠይቀዋል። “ኦሮሚያ ውስጥ አናርኪ ለመፍጠር ገንዘብ በመርጨት የሚሰራ ስራ አለ ። እንስራለን ብለን ያቀድነውን ስራ ትተን ሌላውን ስራ እድንሰራ ነው እየተፈለገ ያለው” ያሉት አቶ ለማ፣ …ዛሬም ችግሮች ቢኖሩም ቄሮዋች ከጎናችን ሆነው እየታገሉ ናቸው “ብለዋል። አሁንም የኦሮሞ ነፃ አውጪ በሚል ስም የጦርነት አዋጅ እያወጀ ያለው አካል ድርጊቱን ቆም ብሎ እንዲያስቡበት እና ወደትክክለኛው መንገድ እንዲመለስ የመከሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ይሄን ያሉት ለመንግስት ችግሩን መቆጣጠር ከባድ ሆኖበት ሳይሆን ወዳልተፈለገ የኃይል እርምጃ ከመግባት ይልቅ ጉዳዩ በሰላም እልባት እንዲያገኝ ካላቸው ፍላጎት በመነሳት እንደሆነ አብራርተዋል።ኦቦ ለማ መገርሳ ንግግራቸውን ሲቋጩም፦”ጭቆና መሸከም አንችልም ብለን ታግለንና መስዋእትነት ከፍለን ወደ ነጻነት መንገድ መሸጋገር ጀምረናል..ዛሬስ ነፃነትንም መሸከም የማንችል ህዝቦች ነን እንዴ..?”ሲሉ ጠይቀዋል።
Esat
Monday, July 9, 2018
Eritrea and Ethiopia have signed a Joint Declaration of Peace and Friendship
Wednesday, July 4, 2018
Skirmish broke out between Sudanese soldiers and Ethiopian farmers along the border
A skirmish along Ethio-Sudanese border between Ethiopian farmers and Sudanese border soldiers reportedly left five Ethiopian farmers dead and several others injured from both sides.
Amhara Mass Media Agency( AMMA), the regional state media, confirmed that the skirmish involving Sudanese Border Security and Ethiopian farmers happened this morning in Metema district of the zone along Delelo Agricultural investment land. The source added that there were casualties on both sides but did not indicate the numbers.
ESAT, US based Ethiopian News outlet, cited sources from Metema region to report that an unprovoked attack by Sudanese soldiers left at least five Ethiopian farmers dead but did not report about casualties on the side of Sudanese forces.
Ethiopian soldiers are reportedly deployed to the border region where the skirmish happened and that a relative calm is restored.
Based on AMMA report the skirmish is over cultivable land that Ethiopian farmers used to farm. Head of West Gonder Zone, Zelalem Lijalem, is quoted as saying “The cause for the conflict along the Ethiopian and Sudan border is claim over the arable land.” What sparked the conflict is, says the report, that Sudanese soldiers restricted Ethiopian farmers not to plow land which they have been allegedly farming in the past. AMMA also cited Lijalem, the top government authority in the region, as saying that Ethiopian farmers used to farm for a long time and that they have explained the matter to Sudanese authorities.
Neither Sudanese government authorities nor the Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia has not remarked about the latest conflict so far.
The two governments have a cordial relationship and have numerous bilateral agreements. Sudan also supported Ethiopian position in relation to the talk over the Grand Renaissance Dam.
However, there has been an outcry by Ethiopian farmers in the region for a long time now after the TPLF government allegedly handed over land that belongs to Ethiopia to Sudan. About three or so years ago, TPLF government, which used to be dominant in the Federal government while representing only five percent of the Ethiopian population, signed a joint-border security agreement with Sudan and arrangement was made to for a joint-force from the two countries to patrol border areas.
Residents in the Ethiopian side of the region where a skirmish happened this morning seem to believe that TPLF might have instigated the incident. The party was also implicated in numerous internal conflict in different parts of the country in what many believe is an attempt to create a crisis in a way to make the new reformist administration under Abiy Ahmed incapable to handle the situation in the country.
Tuesday, July 3, 2018
ይድረስ ለክቡር ጠቅላይ ሚ/ር ለዶ/ር አብይ አህመድ - Daniel tomas ኢትዮጵያዊ
ይድረስ ለክቡር ጠቅላይ ሚ/ር ለዶ/ር አብይ አህመድ!
እስከዛሬ ድረስ ባደረጉት ቀና ተግባርም ሆነ አስደናቂ ንግግር እንዲሁም ይቅርታ ብዙም አልተደነቅሁም ነበር።ባጭሩ እወድዎት አከብርዎት ነበር እንጅ ለአንዲትም ደቂቃ አምኘዎት አላውቅም ነበር።አይፍረዱብኝ በህወሃት የማስመሰል ፕሮፖጋንዳ ዘመን ያደግሁ ብላቴና ስለሆንኩ ነው።አሁን ግን እርስዎን ማመን እንዳለብኝ ይሰማኛል።ባሁኑ ሰዓት እርስዎን አለማመንና እርስዎን መተቸት ከማናቸውም አይነት ኢትዮጵያዊ ዜጋ አይጠበቅም።ስለዚህ በሰውኛ ሚዛን 99%አምኘዎታለሁ።99% ወድጀዎታለሁ።
ይህ ሙሉ እምነትና ሙሉ መውደድ አይደለምና እባክዎ100% እንድወድዎትና እንዳምንዎት አንዲት ጩኸት በመስማት ይርዱኝ!?አይዞዎት ከባድ የሆነ ጥያቄ አይደለም የምጠይቅዎ።
እርስዎ ኢትዮጵያን ልክ እንደ እኔ እስከመጨረሻው እንዲወዱና እንዳከበሩዋት እንዲያልፉ ነው የምፈልገው።
ሆኖም ስጋት አለኝ።ዘወትር የሚረብሸኝ አንድ ስጋት!ይህንን ስጋቴን ላካፍልዎ የደፈርኩትም፤"ብረት ግሪስ እንዲቀባ ከፈለገ መጮህ አለበት!ብረት ጩኸት ካላሰማ ግሪስ የሚቀባው የለም!ስለዚህ መንግስት መልእክታችሁን እንዲሰማችሁና ችግሩን እንዲቀርፍ ከፈለጋችሁ መጮህ አለባችሁ!ያልጮኸ ብረት ግሪስ አይቀባም!ስለዚህ ጩኹ"በማለት በአርቲስቶች ስልጠና ወቅት ሲናገሩ ስለማሁ ነው።ስለዚህ የብዙዎቻችን ምናልባትም የመላው ዜጋ ጩኸት ነውና ይስሙን!
በግልጽ እንደሚያውቁት በእርስዎ ስልጣን መያዝ ምእራባውያኑ ደስተኞች ናቸው።ምናልባትም ከኛ እኩል ደስተኞች ሳይሆኑ አይቀርም።
ህወሃቶች ኢትዮጵያን እድሜ ልካቸውን ብቻቸውን ለመዝረፍና አገሪቱን በዘላቂነት ሊያራቁቱ ተዘጋጅተው ስለነበር ምእራባውያኑ የዝርፊያው ተሳታፊና ተካፋይ እንዲሆኑ አልፈቀዱም ነበር።ጅብ ብቻውን መብላት ከመውደዱም በላይ ከራበው የራሱንም ወገን ይበላል።ጅብ ጅብን ስለሚበላው አይደል ከሌላው አውሬ በተለየ ሁኔታ ባለመተማመን ምክንያት ጎን ለጎን ተሰልፎ የሚሄደው?ስለዚህ ጅቦቹ ለአገራቸው አስበው ሳይሆን፤ወከልነው ለሚሉት ለትግራይ ህዝብ አስበው ሳይሆን፤
ብቻቸውን ኢትዮጵያን ለመብላት ሲሉ፤(መብላትስ በልተዋታል) የቀራትን አጥንት ብቻቸውን ለመጋጥ ሲሉ፤አንዱን ብሄር ከሌላው ብሄር በሃሰት ፕሮፖጋንዳቸው እያጋጩ ዝርፊያቸውን ቀጥለው ቆይተዋል።ሲቀጥሉም
በብዙ ነገር ለምእራባውያኑ መንገዱን ዘግተውባቸው ነበር።
እርስዎ ደግሞ ዓላማዎ የተበታተነን አንድ ህዝብ መልሰው ማገናኘትና ማዋሃድ፣በግፍ የታሰሩትን መፍታትና ጸበኞችን ማስታረቅ፣ስትበዘበዝ የኖረችውን፣ በጅቦች የጋራ ጥርስ ውስጥ ገብታ 27 አመት ስትጋጥ የኖረችውን አገር፤ ጅቦችን አባርረው ከቁስሉዋ እንድታገግም ማድረግና ልጆቹዋን አስተባብረው እናታቸውን እንዲጠብቁና ከጥቃት እንዲከላከሉ ማድረግ፣ወደ ታላቅነቱዋ መመለስና ሰላም አስፍኖ በአንድነት መኖርን ነው።ለዚህም በማናቸውም አይነት መንገድ የምእራባውያን እገዛ ሊያስፈልግዎ ይችላልና እነሱን ወደጎን ማድረግ ለጊዜውም ቢሆን ላይችሉ ይችላሉ።እነሱም በአገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባታቸው አይቀርም።ግድ የለም ይግቡ።ነገር ግን ክቡርነትዎ አንድ ነገር ማስታወስ ይጠበቅብዎታል!እነሱ ማለት በእርስዎ የስልጣን ዘመን የግብረሰዶማውያንን ባንዲራ በምድራችን በመዲናችን ያውለበለቡ ናቸው!በወቅቱ እርስዎ ውጥረት ላይ ነበሩና ልብ ላይሉት ይችላሉ።ሜይ 17 2018 በአዲስ አበባ የተፈጸመው ተግባር ለኛ ለኢትዮጵያውያን እጅግ የሚያሸማቅቅ የድፍረት ተግባር ነበር።
አባቶቻችን በነጭ አንገዛም ሲሉና መስዋእት ሆነው ይችን የተከበረች አገር ነጻ አድርገው ሲያስረክቡን፤የነጮችን ሴራና ዝርፊያ ጠልተው ብቻ አይደለም።በዋናነት ሐይማኖት እንዳይፈርስ፣ባህል እንዳይደፈርስ፣ወግ እንዳይገሰስ፣ማንነት እንዳይቆሽሽ፣ሉአላዊነት እንዳይሸጥና እንዳይለወጥ፣ዜጎች በገዛ አገራቸው ባእድ እንዳይሆኑና ያለፍላጎትና ያለእምነታቸው በባእዳን ትእዛዝና ፍላጎት እንዳይነዱ በሚል ነው!ስለዚህ አገራቸውን በፍቅር አንድ ሆነው ከጠላት ተከላክለው አቆይተው እርስዎን በወንበራቸው ላይ አስቀምጠዋል።
ይችን ቅድስትና ምስኪን አገር መምራት የሚችለውና መምራትም ያለበት ደግሞ እንደ እርስዎ አይነት አገሩንና ህዝቡን የሚወድ፣ጅቦችን ጅብ ጀግኖችን ጀግና የሚል፣በጀግኖች አባቶቹ የሚኮራ፣አባቶቹን እናቶቹን፣እህቶቹንና ወንድሞቹን ከእነ ጥፋታቸው ይቅር ብሎ፤ የራሱ ወገኖች፣ የራሱ አካሎች መሆናቸውን ቆጥሮ የሚያከብር፣ወንበራቸውን ቤተመንግስታቸውን የሚያከብር፣ከማጠልሸት ይልቅ የሚያድስ፣ከማፍርስ ይልቅ የሚገነባ፣ጥሩ ስብእናና ፍቅር ያለው ኢትዮጵያዊ ብቻ ነው።ስለዚህ እርስዎ ወንበሩ ይገባዎታልና ይዘውታል።ሲይዙትም ኢትዮጵያን መያዝዎ ነው።ኢትዮጵያን ሲይዙም ህዝቡን መያዝዎ ነው።ህዝብ የሚባለው ደግሞ አምኖበትና ተስማምቶ ራሱ ባወጣው ህግ የሚመራ ማለት ነው።የሚወጣው ህግ ደግሞ የአገሪቱን ክብርና ህልውና የማያስደፍር ህግ ነው።የህዝቦችን ባህል፣ ልማድ፣ ወግና ሐይማኖት የማይዳፈር ነው።
ኢትዮጵያ ደግሞ በሙስሊምም በክርስቲያንም ቅዱሳት መጻሕፍት የተጠቀሰችና የተከበረች፤ ስሙዋም በመልካም ተደጋግሞ የተነሳ ቅድስት አገር ናት።
በመሆኑም የምእራባውያን ፍላጎት ስለሆነ ብቻ፣እርዳታና ብድር ስለሚሰጡ ብቻ፣በተለያየ ዓለማዊ ህጋቸው፤ በየዘርፉ ከየአገራቱ ጋር ስለተሳሰሩ ብቻ፣ህጋቸውን ህጋችን አድርገው መቀበል እንደሌለብዎት ሳስጠነቅቅዎና ስጠቁምዎ፤ህጋቸውን እንደማይቀበሉት ከመገመት ጋር ነው።
ይህን የግብረሰዶማውያን ዓላማ በህጋችን ውስጥ እንዳያካትቱትና ብኩርናችንን በምስር ወጥ እንዳይሸጡብን እንደ አንድ ዜጋ በጽኑ ላሳስብዎትና ላስጠነቅቅዎት እፈልጋለሁ።
ጸሃፊው እንዳለው፤"ዓለማችን ብዙ የሚያስጨንቃት ነገር እያለ፤የዓለም ሃያላን አገራት መሪዎች ግን ብእርና ወረቀት ይዘው ከፍ ያለ በጀትም መድበው ስለዚህ አስጸያፊ ተግባር ሌት ተቀን የሚወያዩትና በየህጋቸው እያጸደቁ የሚገኙት፤ ፍላጎቱ የህዝብና የየአገራቱ ሆኖ ሳይሆን፤ የሌላ እርኩስ መንፈስ ኣላማ አስፈጻሚዎች ስለሆኑ ብቻ ነው"
ያ ባይሆን ኖሮ በሐይማኖትም፣በህገ ልቦናም፣የተከለከለውን፣በ
ፈጣሪ ዘንድ ያልተፈቀደውንና የተወገዘውን፣ሌላው ቀርቶ እንደ ሰው ማሰብ አይችሉም የምንላቸው እንስሳት እንኩዋን የማይፈጽሙትን፤ የተመሳሳይ ጾታ ወሲባዊ ግንኙነትን ባላቀነቀኑት ነበር።የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን ባልደገፉት የህግ ከለላም ባልሰጡት ነበር!ሰዎችንም ወደዚህ መስመር እንዲቡ ባልገፋፉ ነበር።
እነሱ ግን አላረፉም።በዚህ ጉዳይ አምርረው የሚገኙ ሆነዋል!ዳቦ ያጣውን በዳቦ፣ስልጣኔ ያጠረውን በስልጣኔ፣ፍትህ ያጣውን በፍትህ እያሉ ሁሉም ህዝብና መንግስታት ላይ ጫና እያሳደሩ ነውና ወደኛም አገር ረጅም እጃቸውን ሰደው በዚህ ጉዳይ ላይ ጫና መፍጠራቸው አይቀርምና ከወዲሁ ይዘጋጁበት እላለሁ።
በዓመታዊ ክብረ በአላቸው ላይም በዘንድሮው ዓመት እንዳደረጉት፣ ባንዲራቸውን በዚች አገር እንዳውለበለቡት፣በዚያውም የማለማመድ ተግባራቸውን እንደጀመሩት፤በቀጣይ ተከታታይ ዓመታትም አጠናክረው መቀጠላቸው አይቀርምና ሙሉ እምነት የጣለብዎትን ህዝብዎን በዚህ በኩል እንዲታደጉትና ጠንካራ ተከላካዩ ሆነው እንዲገኙለት በኢትዮጵያ ስም እጮሃለሁ።
"ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ"የሚሉ መሪ ነዎትና፤ኢትዮጵያ በፈጣሪ ትባረክ ዘንድ ይህን የእርኩሰት ተግባር ከፊት ሆነው እንዲከላከሉ አደራ እልዎታለሁ።
መልካም የስራ ዘመን ይሁንልዎ።
በዚህ መልእክት የምትስማሙ ወገኖች ሼር በማድረግ ተባበሩ።
Daniel tomas ኢትዮጵያዊ
Recent Articles
Recent Video Uploads
Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube
Ethiopia Today
- Active a minute ago with many
- videos

