Monday, February 20, 2017

‹‹የምርጫ ቦርድ አካሄድ የተለመደ በመሆኑ የሚያስደንቅ አይደለም›› ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት

- ‹‹በፓርቲው አባላት መካከል ምንም ዓይነት ልዩነት የለም››  አቶ የሺዋስ አሰፋ
ላለፉት አራት ወራት ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ ሕጋዊ መሪ (ሊቀመንበር) እኔ ነኝ እኔ ነኝ›› በማለት ሲወዛገቡ በከረሙት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትና አቶ የሺዋስ አሰፋ ላይ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 8 ቀን 2009 ዓ.ም. ውሳኔውን አሳወቀ፡፡
ቦርዱ ውሳኔውን ያስታወቀው የሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 10(6)ን በመጥቀስ፣ እነ አቶ የሺዋስ አሰፋ መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም. በፓርቲው ኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን በኩል፣ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ በመጥራት ምርጫ ማካሄዱንና አቶ የሺዋስን ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡን ያሳወቀበትን ሪፖርት መርምሮ ነው፡፡
ከላይ የተጠቀሰው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ እንደሚያስረዳው፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ አልተወጣም ብሎ ካመነ፣ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የመተማመኛ ድምፅ ሊሰጥ ይችላል፡፡ ነገር ግን ብሔራዊ ምክር ቤቱ የመተማመኛ ድምፅ ከነፈገው፣ በኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን በኩል አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ በመጥራት ችግሩ እንዲፈታ ማድረግ እንደሚችል ያብራራል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ እነ አቶ የሺዋስ ያደረጉት የምርጫ ሒደትን ሲመረምር፣ በሕጉና በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት መፈጸማቸውን በማረጋገጥ መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም. የተደረገው ጠቅላላ ጉባዔ፣ በቦርዱ ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን፣ በቦርዱ ጸሐፊና የጽሕፈት ቤቱ ዋና ኃላፊ በአቶ ነጋ ዱፊሳ ፊርማ ወጪ የተደረገው ደብዳቤ ያሳያል፡፡
ምርጫ ወይም ጠቅላላ ጉባዔው የተደረገው ኮረም ሳይሟላ፣ ታዛቢዎች በሌሉበትና የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ ተጥሶ መሆኑን በመጥቀስ የፓርቲው ሕጋዊ ሊቀመንበር መሆናቸውን በመግለጽ ሲከራከሩ ስለነበሩት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ቦርዱ በውሳኔው ላይ ያለው ነገር የለም፡፡
ቦርዱ በውሳኔው እሳቸውን አስመልክቶ ምንም አለማለቱን አስመልክቶ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት እንደተናገሩት፣ የምርጫ ቦርድ አካሄድ የተለመደ ነው፡፡ ‹‹አንድና ሁለት በመቶ ያህል ተስፋ ያደረግነው ሕዝቡን አስበው እውነተኛ ውሳኔ ይሰጣል የሚል ነበር፡፡ በመሆኑም የሚያስደንቅ አይደለም፡፡ እኛ የመጀመሪያ ሳንሆን በቅንጀት፣ በኦብኮ፣ በአንድነትና በመኢአድ ላይ የተፈጸመው በእኛም ላይ በመድረሱ አያስገርመንም፤›› ብለዋል፡፡
የመሠረቱት ፓርቲ እንደ ሌሎቹ ፓርቲዎች በሁለትና በሦስት አባላት መቀለጃ ሆኖ እንዳይቀጥል በሕግ ወይም ጠቅላላ ጉባዔው በሚወስነው ሁኔታ ለመታገል፣ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2009 ዓ.ም. በሚያደርጉት ስብሰባ ለሕዝብ እንደሚያሳውቁ አስረድተዋል፡፡
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ ተከትሎ ሰማያዊ ፓርቲ ዓርብ የካቲት 10 ቀን 2009 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ 15 ቀናት በማይፈጅ የውሳኔ ሐሳብ ከአራት ወራት በላይ ቦርዱ ሳያሳውቅ በመቅረቱ አላስፈላጊ ውጣ ውረዶች መከሰታቸውን አዲሱ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ ተናግረዋል፡፡ ቦርዱ ዘግይቶም ቢሆን የሰጠው ውሳኔ ሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንቡንና የፓርቲዎች የምርጫ ሕግን በማክበር የሚሠራ መሆኑን ያረጋገጠ በመሆኑ፣ ‹‹የቀድሞ አመራሮችና አንዳንድ አባላት እየፈጠሩት በነበረው ሁከት ግራ ለተጋቡ ደጋፊዎቻችን ጥሩ ምላሽ ነው፤›› ብለዋል፡፡
በፓርቲው ውስጥ መከፋፈል ስለነበር አባላትና ደጋፊዎች ግራ ተጋብተው መክረማቸውንና በፓርቲው ህልውና ላይ መተማመኛ ስለመኖሩ የተጠየቁት አቶ የሺዋስ፣ በፓርቲው ውስጥ መከፋፈል ያለ ለማስመሰል መሞከሩን አስረድተዋል፡፡ ነገር ግን አራቱም አካላት ማለትም ጠቅላላ ጉባዔው፣ ብሔራዊ ምክር ቤቱ፣ ሥራ አስፈጻሚውና የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽኑ በሙሉ እንዳሉ መሆናቸውን አክለዋል፡፡  
በሁሉም ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ በፓርቲ አባላት መካከል ምንም ዓይነት ክፍተትም ሆነ ልዩነት እንደሌለ አቶ የሺዋስ ገልጸዋል፡፡
ሌላው አቶ የሺዋስ የተናገሩት በገዢው ፓርቲና 22 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያደረጉትን ድርድር በሚመለከት ነው፡፡
በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃንና የኅብረተሰብ ክፍሎች ‹‹ውይይትና ክርክር›› እየተደረገ እንደሆነ የሚናገሩት ስህተት መሆኑን የገለጹት አቶ የሺዋስ፣ ኢሕአዴግና ተቃዋሚ ፓርቲዎች አሁን እየተዘጋጁ ያሉት ‹‹ድርድር›› ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ውይይት የሚዲያ ተግባር ሲሆን፣ ክርክር ደግሞ በምርጫ ወቅት የሚደረግ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ‹‹በእርግጥ ድርድር በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ ቢሆንም እኛ ግን 22 ሆነን ጀምረነዋል፤›› ብለዋል፡፡
ከ2002 ዓ.ም. ጀምሮ በገዢው ፓርቲና በተቃዋሚዎች መካከል ድርድር ተደርጎ እንደነበር ያስታወሱት አቶ የሺዋስ፣ አንድም ጊዜ የተገኘ ውጤት እንደሌለና አሁንም የተለየ ውጤት ይገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡
ኢሕአዴግን ሁሉም ፓርቲዎች ለድርድር ያልጠየቁበት ጊዜ እንዳልነበርና ምንም ምላሽ ሰጥቶ እንደማያውቅ ያስታወሱት አቶ የሺዋስ፣ የሕዝብ ጥያቄ አይሎ ሲነሳ ግን በሩን መክፈቱን አስረድተዋል፡፡ የመደራደርን ሐሳብ በቅድሚያ ያነሱት የአገሪቱን ሁኔታ የተመለከቱ አቅጣጫው ያስፈራቸው የውጭና የአገር ውስጥ ሽማግሌዎች ሆነው ሳለ፣ ኢሕአዴግ ግን ሐሳቡን ራሱ እንዳመነጨው በማድረግ ‹‹እንደራደር›› ማለቱ ተገቢ አለመሆኑንና ዕውቅናውን ለአገር ሽማግሌዎች መስጠት እንዳለበትም አስረድተዋል፡፡ ኢሕአዴግ እንደ አንድ ፓርቲ መደራደር እንጂ ሰብሳቢ፣ ታዛቢም ሆነ አደራዳሪ ሊሆን እንደማይችልም አክለዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ እውነተኛ ድርድር ለማድረግና ሕዝቡ በድርድሩ እምነት እንዲያድርበት በቅድሚያ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን መፍታት፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማንሳት፣ ድርድሩን የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል ያሉ ወገኖች ሁሉ እንዲሳተፉ ክፍት ማድረግና ለግልም ሆነ ለሕዝብ መገናኛ ብዙኃን ክፍት መሆን እንዳለበት እምነቱ መሆኑን እንደገለጸ አቶ የሺዋስ አብራርተዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲን ያህል አባላት የታሰሩበት አንድም ተቃዋሚ ፓርቲ እንደሌለም ገልጸው፣ ድርድሩ ከመጀመሩ በፊት ሊፈቱ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ሁሉም ፓርቲዎች ኢሕአዴግን ጨምሮ የሕዝብን ጥያቄ በሚመልስ መንገድ ድርድር ማድረግ እንዳለባቸው ያስታወቁት አቶ የሺዋስ ሕዝቦች ባነሱት ጥያቄ ምክንያት የሞቱ፣ የተፈናቀሉ፣ ወጥተው የቀሩ፣ የታሰሩ ለምሳሌ ዶ/ር መራራ ጉዲና፣ ሁለት ጋዜጠኞች ኤልያስ ገብሩና አናንያ ሶሪ ሌሎችም መፈታት እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ድርድሩ ሙሉ የሚሆነውም ይኼ በተግባር ከተፈተጸመ እንደሆነም አክለዋል፡፡
አሁን ገና ድርድር እንዳልተጀመረና በቀረቡት አጀንዳዎችም ላይ መስማማት እንዳልተቻለ የገለጹት አቶ የሺዋስ፣ አደራዳሪ ማን ይሁን? ታዛቢ ማን ይሁን? የአጀንዳዎች ቅደም ተከተል እንዴት ይሁን? እና ድርድሩ ለየትኛው ሚዲያ ክፍት ይሁን? የሚለው ጥያቄ የካቲት 8 ቀን 2009 ዓ.ም. ምላሽ ሊያገኝ ባለመቻሉ እሳቸውን ጨምሮ ሰባት አባላት ያሉበት ኮሚቴ ተመርጦ፣ የተጠጋጋ ሐሳብ እንዲያቀርብ ለየካቲት 17 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ መያዙን አሳውቀዋል፡፡
ውጤታማ ድርድር ለማድረግና የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት የሕዝብ፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎችና በተቃውሞ ጎራ በያለበት ተሠልፈው የሚገኙ አካላትንና የመንግሥትን ፈቃደኝነት ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን አቶ የሺዋስ አስረድተዋል፡፡ Read more here

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ ሃገራት ሰዎች...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል በዚህ ሳምንት ከ27 በላይ የሚሆኑ ‘ሰላማዊ ሰዎች’ “በመንግሥት ኃይሎች” መገደላቸው ተነገረ
     በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “የመንግሥት ኃይሎች” ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።የደብረሲና ከተማጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19፤ 2016 ዓ/ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን፤ በጥቃቶቹም ከ27 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር...
    June-29 - 2024 | More »
  • AMHARA MASSACRE: A GRIM REMINDER OF ETHIOPIA’S FRAGILE PEACE
     Mariam SenbetBeneath the rich history of Ethiopia lies a disturbing trend of violence that has disrupted the tranquility of its ancient monasteries and the well-being of its inhabitants. On February 22, 2024, a brutal assault resulted in the deaths of four monks within the sacred confines of...
    June-23 - 2024 | More »
  • More details emerging about ethnic Amhara Generals led public meeting in Addis
     On Friday, the Ethiopian Defense Force shared a brief update on its social media page about the meeting that the Deputy Chief of Staff, Abebaw Tadesse,  Defense Operations Manager, General  General Belay Seyoum, and Federal Police Deputy Commissioner, Zelalem Mengiste had with...
    June-23 - 2024 | More »
  • Dr. Fisseha Eshetu’s Claims Under Scrutiny: A Closer Look
     Dr. Fisseha EshetuBy Taye HaileDr. Fisseha Eshetu, the CEO of Purpose Black, has recently made headlines by claiming that he fled Ethiopia out of fear of arrest by the government. He alleges that government agents threatened him and accused him of supporting the group known as Fano. However,...
    June-23 - 2024 | More »
  • በአማራ ክልል ሁለት የጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “በመንግሥት ኃይሎች” ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ
     Bahir Darበአማራ ክልል ምዕራብ እና ምሥራቅ ጎጃም ዞኖች ባለፈው ሳምንት በቀናት ልዩነት ውስጥ ተፈጽሟል በተባሉ ጥቃቶች ከ20 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።ጥቃቶቹ ባለፈው ሳምንት ሰኔ 7 እና 9 ቀራኒዮ እና ጂጋ በተባሉ ከተሞች እንደተፈጸሙ የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ሁለቱም ጥቃቶች የመንግሥት ኃይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ካደረጉ በኋላ ስለመፈጸማቸው ገልጸዋል።እሁድ ሰኔ 9 በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህና...
    June-18 - 2024 | More »
  • ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ
     ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ያቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞች ከእስር ተፈቱ። ዛሬ እና ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ፣ ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው። ሶስቱ ጋዜጠኞች የፌደራል ፖሊስ “ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ በእስር እንዲቆዩ” ማድረጉን በመጥቀስ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት ነበር።...
    June-18 - 2024 | More »
  • Jiga, Ethiopia : Government Forces Reportedly Execute 25 Civilians in Following Ambush Loss
     In the latest string of known extrajudicial executions of civilians, the Ethiopian government soldiers reportedly massacred 25 civilians in Jiga, West Gojam, Amhara region of Ethiopia. Residents and Fano forces from the area have confirmed the incident to Ethiopian News outlets based in...
    June-18 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time