በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የህዝቦችን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር ገለፀ። ኢትዮጵያ የህዝቦቿን ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ በለውጥ ሂደት ውስጥ እንደሆነች አንስታል።
ለውጡም መላ የኢትየጵያ ህዝቦችን ባሳተፈ እና ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል ያለው ሚኒስቴሩ፥ እየተካሄደ ካለው የለውጥ እንቅስቃሴም መላው የሀገሪቱ ህዝቦች ተጠቃሚ በመሆናቸው ተሳትፏቸውን በማጠናከር ላይ ይገኛሉ ብሏል።
ሆኖም በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች አልፎ አልፎ የብጥብጥና የሁከት ድርጊቶች እንደሚስተዋሉ አስታውቋል።
እነዚህ ህገወጥ ድርጊቶች በሚስተዋሉባቸው አካባቢዎች የጸጥታ ሃይሉ ከህዝቡ ጋር ሆኖ የማረጋጋት ሥራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ነው የገለፀው።
በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጂግጂጋ ከተማ የተከሰተው ብጥብጥ፣ ቀጥሎም ወደ ሌሎች አንዳንድ የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና በፍጥነት ሊገታ እና ሊታረም የሚገባው ድርጊት መሆኑን አስታውቋል።
የአገር መከላከያ ሠራዊታችን ከሌሎች የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመሆን የተከሰተውን ሁከት በቅርበት ሲከታተል፣ ሁኔታውን ለመቆጣጠርና ህብረተሰቡን ለማረጋጋት ጥረት እያደረገ የነበረ ቢሆንም ብጥብጡ በተፈለገው ፍጥነት ሊቆም አልቻለም ብሏል።
በመሆኑም በክልሉ የህዝቦቻችን ሰላም እና ደህንነት አደጋ ውስጥ እየገባ ያለበት ሁኔታ በመፈጠሩ የመከላከያ ሃይላችን ሁከትና ብጥብጡን በዝምታ የማይመለከት መሆኑንና የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በጥብቅ እንደሚያሳስብ ነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር በመግለጫው ያስታወቀው።
የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል
ከኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ
አገራችን ኢትዮጵያ የህዝቦቿን ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ በለውጥ ሂደት ውስጥ እንደሆነች ይታወቃል። ለውጡም መላ የኢትየጵያ ህዝቦችን ባሳተፈ እና ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል። እየተካሄደ ካለው የለውጥ እንቅስቃሴም መላው የአገራችን ህዝቦች ተጠቃሚ በመሆናቸው ተሳትፏቸውን በማጠናከር ላይ ይገኛሉ።
ሆኖም በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች አልፎ አልፎ የብጥብጥና የሁከት ድርጊቶች ይስተዋላሉ። እነዚህ ህገወጥ ድርጊቶች በሚስተዋሉባቸው አካባቢዎች የጸጥታ ሃይሉ ከህዝቡ ጋር ሆኖ የማረጋጋት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል በጂግጂጋ ከተማ የተከሰተው ብጥብጥ፣ ቀጥሎም ወደ ሌሎች አንዳንድ የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና በፍጥነት ሊገታ እና ሊታረም የሚገባው ድርጊት ነው።
የአገር መከላከያ ሠራዊታችን ከሌሎች የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመሆን የተከሰተውን ሁከት በቅርበት ሲከታተል፣ ሁኔታውን ለመቆጣጠርና ህብረተሰቡን ለማረጋጋት ጥረት እያደረገ የነበረ ቢሆንም ብጥብጡ በተፈለገው ፍጥነት ሊቆም አልቻለም።
በመሆኑም በክልሉ የህዝቦቻችን ሰላም እና ደህንነት አደጋ ውስጥ እየገባ ያለበት ሁኔታ በመፈጠሩ የመከላከያ ሃይላችን ሁከትና ብጥብጡን በዝምታ የማይመለከት መሆኑንና የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በጥብቅ ያሳስባል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር
ሃምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም.
Sunday, August 5, 2018
ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር ገለፀ
የሶማሌ ክልል ከኢትዮጵያ ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው
የሶማሌ ክልል (ክልል 5) ከኢትዮጵያ ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። ዋና ከተማው ጅጅጋ ነው። 279,252 ካሬ ኪ.ሜ. ቦታ ሲሸፍን በ1991 የሕዝብ ብዛቱ 3,602,000 ነበር። ባሁኑ ስአት የሕዝብ ብዛት በአጠቃላይ 5,148,989 በላይ ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በጣም ብዙ የሶማሌ ብሔረሰቦች ይገኙበታል። በ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ሶማሊያ ቦታውን በወውረር ከኢትዮጵያ ጋር ጦርነት አስነስታ ነበር። ከነዚህም ዋነኛው የኦጋዴን ጦርነት ነው። ርዕሰ ከተማ ጅጅጋ ሲሆን ጅጅጋ በምስራቅ ኢትዮጵያ የሚገኝ ከተማ ነው። ከተማው ከሐረር 80 ኪ.ሜ. ይርቃል። በቀድሞው ሐረርጌ ክፍለ-ሀገር የሚገኝ ከተማ ሲሆን አሁን የሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ነው። በ1994 እ.ኤ.አ. ከተማው 56,821 ሰዎች ነበሩት። በ1998 ማዕከላዊ የስታትስቲችስ ባለስልጣን እንደተመነው ጅጅጋ የ98,076 ሰው መኖሪያ ስትሆን ከነሱም 50,355 ወንዶችና 47,721 ሴቶች ይገኙበታል። ከተማው በ9°10' ሰሜን ኬክሮስ እና 42°48' ምስራቅ ኬክሮስ ይገኛል። የሶማሌ ፕሬዚዳንት ሞሐሙድ አብዲ ኦማር («አብዲ ኢለይ») ይባላሉ። በክልሉ የሱማሌ ብሔር ሲገኙ የሶማሌ ብሔር ከኢትዮጵያ ሱማሎ ውጭም በአፍሪካ ቀንድ ይገኛሉ። ሱማሊኛ ቋንቋቸው ነው። ጠቅላላ ብዛታቸው ከ10 እስከ 20 ሚሊዮን የሚገመት ሲሆን እነዚህም በሶማሊያ (ከ8 ሚሊዮን በላይ)፣ ኢትዮጵያ ሱማሌ (ከ3 እስከ 5 ሚሊዮን)፣ ጅቡቲ (250,000)፣ ሰሜን-ምስራቅ ኬንያ (240,000)፣ እና በሌሎች ውጭ ሀገሮች ይገኛሉ። ዋና ሃይማኖታቸው ሱኒ እስልምና ነው።
ሶማልኛ ቋንቋ ኩሺቲክ ተብሎ በሚታወቀው የቋንቋ መደብ የአፍሮ-እስያ ቤተሰብ የሚካለል ቋንቋ ነው። በአፍሪካ ቀንድ በሚገኙ አገሮች፥ በኢትዮጵያ ፥ ጅቡቲ፥ ሶማሌና ኬንያ፥ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ተናጋሪዎች አሉት። በ1964፥ በዚአድ ባሬ መንግስት አነሳሽነት፥ ለመጀመሪያ ጊዜ በ ላቲን ፊደል መጻፍ ጀመረ።
Saturday, August 4, 2018
በጂግጂጋና ሌሎች የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በፍጥነት ሊገታ ይገባል:- ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር
በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል በጂግጂጋ ከተማ ሌሎች አንዳንድ የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና በፍጥነት ሊገታ እና ሊታረም የሚገባው መሆኑን የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
መከላከያ ሠራዊቱ ከሌሎች የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመሆን የተከሰተውን ሁከት በቅርበት ሲከታተልና ሁኔታውን ለመቆጣጠርና ህብረተሰቡን ለማረጋጋት ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጅ እንደሚወስድ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል፡፡
የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ ከመንግስት ኮሙኒከረሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ደርሶናል እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ የህዝቦቿን ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ በለውጥ ሂደት ውስጥ እንደሆነች ይታወቃል።
ለውጡም መላ የኢትየጵያ ህዝቦችን ባሳተፈ እና ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል።
እየተካሄደ ካለው የለውጥ እንቅስቃሴም መላው የአገራችን ህዝባችን ተጠቃሚ በመሆናቸው ተሳትፏቸውን በማጠናከር ላይ ይገኛሉ።
ሆኖም በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች አልፎ አልፎ የብጥብጥና የሁከት ድርጊቶች ይስተዋላሉ።
እነዚህ ህገወጥ ድርጊቶች በሚስተዋሉባቸው አካባቢዎች የጸጥታ ሃይሉ ከህዝቡ ጋር ሆኖ የማረጋጋት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል በጂግጂጋ ከተማ የተከሰተው ብጥብጥ፣ ቀጥሎም ወደ ሌሎች አንዳንድ የክልሉ ከተሞች የተዛመተው ሁከት በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና በፍጥነት ሊገታ እና ሊታረም የሚገባው ድርጊት ነው።
የአገር መከላከያ ሠራዊታችን ከሌሎች የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመሆን የተከሰተውን ሁከት በቅርበት ሲከታተልና ሁኔታውን ለመቆጣጠርና ህብረተሰቡን ለማረጋጋት ጥረት እያደረገ የነበረ ቢሆንም ብጥብጡ በተፈለገው ፍጥነት ሊቆም አልቻለም።
በመሆኑም በክልሉ የሚኖሩ ህዝቦቻችን ደህንነት እና ሰላም አደጋ ውስጥ እየገባ ያለበት ሁኔታ በመፈጠሩ የመከላከያ ሃይላችን ሁከትና ብጥብጡን በዝምታ የማይመለከት መሆኑንና ችግሩንም ለመቅረፍ ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በጥብቅ ማሳሰቡን የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
የአብዲ ዒሌ እብደት
Friday, August 3, 2018
ተስፋ ሰጭው የሳይንስ ትግበራ -የሮኬት ሙከራ
‹‹የተማሪዎችን ፈጠራ በእውቀት እና በገንዘብ የምንደግፍበት ወቅት ነው›› የባሕርዳር ሳይንስ ማበልፀግያ ማዕከል፡፡
ሳይንስ ለችግሮች መፍትሄ ለማምጣት የምንጥርበት የእውቀት እና ክህሎት መድረሻ ነው። የሁሉም ስኬታማ ሳይንስ መነሻው ችግር ፣ ትንንሽ ሙከራዎች እና የሚያድጉ ፍላጎቶች ናቸው።
የተማሪዎቹ ግኝት ከሶስት ዓመታት በላይ የወሰደ ሳይንሳዊ ግኝት ነው የሚሉት የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋየ ሽፈራው ሳይንስን መተግበር እንደተጀመረ ማሳያ ነው ይላሉ።
Recent Articles
Recent Video Uploads
Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube
Ethiopia Today
- Active a minute ago with many
- videos







