Saturday, June 2, 2018

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መነሳት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሰጡት መግለጫ

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መነሳት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሰጡት መግለጫ
የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሀገር እና ህዝብ ያሉበትን ነባራዊ እውነታ እና በቀጣይም እንደ ሀገር ሊገጥም ይችላል ተብሎ የሚገመት አደጋን ለመከላከል በመደበኛው ህግ እና አሰራር የማይቻል ሆኖ ሲገኝ የሚመርጥ አስገዳጅ አማራጭ ነው።
ሃገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት አመታት ባጋጠማት የፖለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለሁለተኛ ጊዜ እንዲታወጅ ተደርጓል።
ይህንን ተከትሎም በመንግስት ዘንድ በተከናወነው ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እና በተከታታይ በተወሰዱ እርምጃዎች ህዝቡ መንግስት ባለው ችግሮችን የመፍታት ፍላጎት እና አቅም ላይ ተስፋን ሰንቋል፤ በዚህም ምክንያት ህዝቡ የሰላሙ ዘብ በመሆን ላለፉት ሁለት ወራት በሀገራችን አንጻራዊ የሰላም ንፋስ መንፈስ ጀምሯል።
ዛሬ ያሉበትን እና ነገም የሚደርሱበትን ተፈጥሯዊ የህይወት ኡደት- ሰላማዊ የመሆኑን እንዴትነት ባለማመን ውስጥ መኖር በሰርክ ህይወታችንና በእድገት ስኬታችን ላይ የሚያስከትለው አሉታዊ ተጽእኖ እጅግ ብዙ ነው።
ሀገራችን ገብታበት በነበረው ውስብስብ ቀውስ ሳቢያ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን በማወጅ ነገሮች መስመር እንዳይስቱ እና መልሶ ለማረቅም እንዳያዳግቱ ውጤታማ ስራ መስራት ችሏል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጊዜያዊ መፍትሄ እንጂ መደበኛና ዘላቂ ሰላምን የሚያመጣ ባለመሆኑ መንግስትም ይህንኑ በመረዳት የሀገራችን እና የህዝቦቿ ሰላም ከውጫዊ አዋጅ እና ክልከላ ሳይሆን ከዜጎች ፍላጎትና የሰላም ወታደርነት የሚፍለቅ እንዲሆን የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል። በተደረጉት እንቅስቃሴዎችም በመላው ሀገራችን አንጻራዊ ሰላምን ማሰፈን ተችሏል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለነበርንበት ችግር ወቅቱ የሚጠይቀው አማራጭ ውሳኔ ሆኖ ቢያሻግረንም ለማደግ መለወጥ እንደሚታትር ታላቅ ህዝብ ደግሞ ያስከተላቸውና የሚያስከትላቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች መኖራቸው አይካድም።
በመሆኑም የረጅም ዘመን ታሪክ አኩሪ እና በዘመን የተፈተነ የአብሮነት ልክ የማይደራደርበት የሞራል ጥግ ራሱን እና ሌሎችንም ጭምር የሚጠብቅበት ባህላዊ የሰላም መቀነቻ ድግ እና ትላንቱን ዘክሮ፣ ዛሬውን መርምሮ እና ነገውንም ተንብዮ ሀገር አድባሩን በሰላም የሚሞላ ህዝብ ላላት ድንቅ ሀገር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ ከቆየችው በላይ ትቆይ ዘንድ አይገባትም።
እንደ ኢትዮጵያ ላለች የዲፕሎማቲክ፣ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መናገሻ ለሆነች ሀገር የአሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቆይታን ለማብቃት የሚደረግ ጥረት እና የጋራ ርብርብ አንድምታው ብዙ ነው።
መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስለማንሳት እና ህዝቡንም ወደ መደበኛው የአስተዳደር፣ የህግ እና የፍትህ መስመር ስለመመለስ ሲያስብ አዋጁን ለማወጅ ካስገደዱት ተግዳሮቶች አንጻር ያለውን ችግር በተመለከተ የመፍትሄውን ቁልፍ በማግኘት በኩል ሙሉ እምነቱ ያለው በህዝቡ እና በህዝቡ ላይ ብቻ ነው።
መንግስት እና ህዝብ አዋጁን በማንሳት የሀገራችንን ሰላም እና የዜጎችን ደህና ወጥቶ ደህና የመግባት መብት፣ ምኞት እና ጸሎት እውን ለማድረግ በሚታትሩበት ወቅት ጉዳዩን ወደ ሌላ አቅጣጫ ለመግፋት እና ዞረን ተዟዙረን የቀውስ አዙሪት ውስጥ እንድንዳክር ለማድረግ የሚጥሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ሊኖሩ የመቻላቸውን ነገር ለአፍታም ቢሆን ቸል ልንል አይገባም።
መንግስትም ስጋቱን እንደ ስጋት የሚጋራው ቢሆንም እንደ ታላቅ ሀገር እና እንደ ኩሩ ህዝብ ከአስጊው ስጋት ይልቅ ከኩሩው ህዝብ እምነት ጋር በመደመር ነገን ብሩህ ለማድረግ መስራት የመንግስት ምርጫ ሆኗል።
ህዝባችን በገዛ ፈቃዱ መዳፉ ውስጥ ያኖረውን ሰላም ከሌላ መዳፍ ውስጥ አኑሮ ያለፈቃዱ የሚሰጋ- ያገሩን ሰላም የሚያናጋ ሳይሆን የሰላሙ ዘብ ራሱ መሆኑን በማመን ሀገር- ቀኤውን ከቀውስ የሚጠብቅ እንደሚሆን መንግስት በጽኑ ያምናል፤ መንግስት በተለያዩ ጊዜያት የህዝባችን ጥያቄ ሆነው የቆዩ የተለያዩ ጉዳዮች ሁነኛ ምላሽ ያገኙ ዘንድ ያለመታከት ይሰራል።
ከችግሮቹ ስፋት እና ጥልቀት አንጻር ህዝብ በሚፈልገው ልክ እና መጠን ለሁሉም ጥያቄዎች አሁናዊ ምላሽ ማግኘት አዳጋች ቢሆንም መንግስት የመጨረሻውን የፍጥነት እና የትጋት ልክ ተጠቅሞ ከኢትዮጵያ ሰማይ ስር ነገሮች ሁሉ መልካም እንዲሆኑ ከህዝቡ ጋር ይረባረባል።
ምንም እንኳን ዛሬ ለነገ መሰረት የመሆኗ ነገር ባያጠያይቅም ዛሬ ሰላም መሆን ማለት ግን ነገም ሰላም ትሆናለች የሚል ዋስትናን አይሰጠንም፤ ነገ ሰላም የምትሆነው በሁላችንም ጥረት እና ዛሬ ላይ ለነገ በምንጥለው የፍቅር መሰረት ብቻ ነው።
በመሆኑም መንግስት ህዝብን እና ህዝብን ብቻ አምኖ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የማንሳት ውሳኔ ላይ ሲደርስ ህዝባችንም በሀገሩ ምድር ሁሉ ላይ የሁልጊዜም የሚሆነውን እና ከየሰው አእምሮ የሚመነጨውን ተፈጥሯዊ የሰላም አዋጁን በህብረት እንደሚያውጅ እምነቴ የጸና ነው።
ይህ ሲሆን ብቻ በእርግጠኝነት ነገ ከዛሬ የተሻለች ትሆናለች፤ ሀገራችን እና ህዝባችን ዘላቂ ሰላም እና የማያቋርጥ ለውጥ መገለጫቸው እንዲሆን ካስፈለገ መተኪያ የሌለው የሁሉም ነገር መሰረት እና ካስማ ሰላም እና ሰላም ብቻ ነው።
በዚህ ሀሳብ መነሻነትም ባለፉት ወራት በሀገራችን ታውጆ የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተነሳ መሆኑን እያሳወኩ በቀጣይም የሀገራችን ህዝቦች፣ የፌዴራል እና የክልል የጸጥታ ሀይሎች፣ በየደረጃው የምንገኝ የፌዴራል እና የክልል የስራ ሀላፊዎች፣ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አባሎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሀይማኖት አባቶች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች እና የሚድያ ሰዎች፣ የሀገራችን የቅርብ ወዳጆች እና አጋሮች፣ የሀገራችን ምሁራን እና የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ የሀገራችን ጉዳይ ያገባናል በማለት የዚህች ሀገር ደግ ቀን እንዲነጋ በተለያዩ መንገዶች የበኩላችሁን እያደረጋችሁ ያላችሁ በውጪ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ከምንም በላይ ለዚህች ሀገር ብልጽግና እና ለህዝቦቿም ሰላም ቅድሚያ ሰጥተን በጋራ እንድንረባረብ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
Source: Fana

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopian Health Professionals Association Urges Govt to Promptly Respond to Health Workers' Demands Amid Pre-Strike Demonstrations
     Dagmawi Melnilik Hospital, which was later upgraded to a referral hospital, is the nation’s first hospital, built in 1909.Addis Standard (Addis Ababa)As health professionals across Ethiopia stage pre-strike demonstrations demanding improved salaries, benefits, and working conditions, the...
    May-13 - 2025 | More »
  • Commentary: Why Ethiopian university lecturers' strike failed: A cautionary tale for health professionals
     The moment of release of the detained teachers’ coordinators, greeted by fellow teachers awaiting their return. Photo: Provided by the writerIn 2022, Ethiopian university lecturers launched a year-long social media campaign  and subsequent threat for indefinite...
    May-13 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-08 - 2025 | More »
  • ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ
     የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ...
    May-08 - 2025 | More »
  • በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት
     ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ...
    May-05 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-05 - 2025 | More »
  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው  ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time