Tuesday, October 10, 2017

በአዳማ ከተማ ሁለት ህፃናት በዱር እንስሣት ተበልተው ተገኙ፡፡

በአዳማ ከተማ ሁለት ህፃናት በዱር እንስሣት ተበልተው ተገኙ፡፡
አንደኛዋን የሁለት ዓመት ህፃን ከእናትና አባቷ እቅፍ ነጥቆ የበላት ጅብ መሆኑን የአዳማ ከተማ ፖሊስ ሪፖርተር ዋና ሳጅን ወርቅነሽ ገልሜቻ ነግረውናል፡፡
የህፃኗ ወላጆች በመድኃኒዓለም ቤተ-ክርስቲያን ጥግ ሁለት ልጆቻቸውን ይዘው በተኙበት ጅቡ ትንሿን እየጐተተ ሲወስዳት በእንቅልፍ ውስጥ ነበሩ ተብሏል፡፡
በድንጋጤ ከእንቅልፋቸው ባነው ጅቡን የተከተሉት ወላጆች ሊደርሱበት እንዳልቻሉ ዋና ሳጅን ወርቅነሽ ነግረውናል፡፡
በተመሣሣይ ማንነቱ ሊለይ ያልቻለ እድሜው 7 ወር የሚገመት ህፃንም በዱር እንስሣት ተበልቶ ትናንት ጠዋት በአዳማ ከተማ ወረዳ ሁለት መገኘቱን ሰምተናል፡፡
ከመበላት የተረፈው የሁለቱ ህፃናት አካል በፖሊስ ተሰብስቦ ለምርመራ ወደ ሆስፒታል ተልኳል ብለዋል ሳጅን ወርቅነሽ፡፡
በአዳማ እንዲህ ዓይነት አጋጣሚዎች ተደጋግመው እየተከሰቱ መሆኑን የነገሩን ሳጅን ወርቅነሽ ህፃናትን ይዘው ለልመና ከቦታ ቦታ የሚዘዋወሩ ሰዎች ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ Read more here

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time