Monday, December 19, 2016

በወልቃይት የማንነት ጥያቄ ሽፋን የሽብር ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠሩ ክስ ተመሠረተባቸው

Capturettt
ከ202 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ንብረቶች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል ተብሏል
የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ጥያቄ በሚባል ሽፋን በኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ መሪነት በአማራ ክልል በተለይ በሰሜን ጎንደር በተለያዩ አካባቢዎች የሽብር ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች፣ ታኅሳስ 5 ቀን 2009 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሠረተባቸው የሰሜን ጎንደር ከተማ ነዋሪዎች አቶ መብራህቱ ጌታሁን፣ ጌታቸው አደመ፣ አታላይ ዛፌና አለነ ሻማ ናቸው፡፡ ከትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን የሰቲት ሁመራ ነዋሪ አቶ ነጋ ባንተይሁንም በክሱ ተካተዋል፡፡
ተከሳሾቹ የአርበኞች ግንቦት ሰባትን የሽብር ተልዕኮ ለማስፈጸም ‹‹የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ ኮሚቴ›› በማለት ራሳቸውን አባልና አመራር ብለው ከሰየሙ በኋላ፣ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን የፕሮፓጋንዳ ኃላፊ አድርገው መሾማቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡
ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንዳብራራው ተከሳሾቹ የማንነት ጥያቄውን ሽፋን በማድረግ፣ ከአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮች ጋር በተለያዩ ተንቀሳቃሽ ስልኮች በቀጥታ ተገናኝተዋል፡፡ በትግራይ ክልላዊ መንግሥትና በወልቃይት አስተዳደሮች ላይ የግድያና የአፈና ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ለወጣቶች የጦር መሣሪያ አስታጥቀዋል፡፡ የታጠቁት ወጣቶች በዳንሻ ከተማ ግለሰቦችን እንዲገድሉ፣ አፍነው እንዲወስዱና በቃፍታ ወረዳ አስተዳዳሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ በማድረግ፣ የዳንሻና ሶሮቃ መንገድ እንዲዘጋ ማድረጋቸውን ክሱ ይዘረዝራል፡፡
በክልሉ በሰሜን ጎንደር ዙሪያ በፀገዴ ወረዳዎች በደባርቅ፣ እንጂባራ፣ ወረታ፣ ደምቢያ፣ መገራ፣ በምዕራብ አርማጭሆ በመተማ ዮሐንስና ዙሪያው ተከሳሾቹ ከመጋቢት 11 ቀን 2008 ዓ.ም. እስከ ነሐሴ 25 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ ባስነሱት አመፅ በመንግሥትና ሕዝብ ተቋማት፣ በግለሰብ መኖሪያ ቤቶች፣ ድርጅቶችና ተሽከርካሪዎች ላይ ከ95.9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት ማድረሳቸውን በክሱ ተጠቅሷል፡፡ በጎንደር ከተማ በሚገኙ ቀበሌዎችም በመንግሥትና በሕዝብ ተቋማትና በተሽከርካሪዎች ላይ ከ10.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውንም አክሏል፡፡
ከነሐሴ 18 ቀን እስከ ነሐሴ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. ደግሞ በምዕራብ ጎጃም በሚገኙ በባህር ዳር ዙሪያ መርዓዊ ከተማ፣ በሜጫ ወረዳ፣ በቡሬ፣ በደጋ ዳሞት አዴት ከተማ፣ በፍኖተ ሰላምና ባህር ዳር ከተማ ከ95.3 ሚሊዮን ብር በላይ በሚገመት ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውንና በድምሩ ከ202 ሚሊዮን ብር በላይ በሚገመት ንብረት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያብራራል፡፡
ተከሳሾቹና ኮሎኔል ደመቀ ሰብሳቢ በመሆን ሰኔ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 ውስጥ በሚገኝ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ግለሰቦችን በመሰብሰብ፣ ‹‹የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ሊሰጠን አልቻለም፡፡ የወልቃይት ፀገዴ የማንነት ጥያቄውን ምክር ቤቱ ወርዶ ሊያየው የሚችለው ደም ሲፈስና ግጭት ሲከሰት ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ እዚህ ተወክላችሁ የተገኛችሁ በሙሉ ወደ መጣችሁበት ቦታ በመሄድ፣ አመፅ በመፍጠርና መንገዶችን በመዝጋት የሽብር ተግባር መፈጸም አለባችሁ፡፡ ይህንን ስታደርጉ ከእናንተም ሆነ ከመንግሥት አካላት ሰው ሊሞት ይችላል፡፡ በዚህ ጊዜ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄያችንን ይፈታልናል፤›› በማለት ቅስቀሳ እንዲያደርጉ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ክሱ ያብራራል፡፡
በወረቀትና በብዕር የሚመጣ ፍትሕ እንደሌለና በሚሄዱበት ቦታ ሁሉ አመፅ እንዲነሳ የሚያደርጉና የሚያስተባብሩ ሰዎችን በመምረጥና በመመልመል፣ የሽብር ተግባሩን እንዲያፋፍሙ ተልዕኮ መስጠታቸውንም ክሱ ይገልጻል፡፡
ተከሳሾቹ በተለያዩ አካባቢዎች ለመለመሏቸው ወጣቶች ገንዘብ በመላክ ከአዲ ረመጽ አካባቢ ጥይት ገዝተው እንዲዘጋጁ ማድረጋቸውን፣ ወጣቶችን እያፈኑ መውሰዳቸውን፣ በተለያዩ ሰዎች ላይ ግድያ መፈጸማቸውንና የግድያ ሙከራ ማድረጋቸውንም ክሱ ያብራራል፡፡
በአጠቃላይ ተከሳሾቹ የማንነት ጥያቄውን እንደ ሽፋን በመጠቀም፣ በውጭ አገር ከሚገኙት ስረበ ጥሩነህ፣ መዓዛው ጌጡና አስማረ ከተባሉት የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮች ጋር በስልክ ግንኙነት በማድረግ የገንዘብ ድጋፍ ሲያገኙ እንደነበር በክሱ ተጠቅሷል፡፡
የአርበኞች ግንቦት ሰባት ታጣቂዎች በኤርትራ በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ በማድረግ፣ የጦር መሣሪያ እንዲገዙና በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን ፀገዴ ወረዳዎች በተለያዩ አካባቢዎች መንገድ በመዝጋት እንዲፈጸም ትዕዛዝ መስጠታቸውን ፍርድ ቤቱ ለተከሳሾቹ ክሱን በንባብ አሰምቷቸዋል፡፡ ተከሳሾቹ የተገለጸውን የሽብር ወንጀል ፈጽመዋል የተባለው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1ሀእናለን)፣ 38 እና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001ን ተላልፈው በመሆኑ፣ የሽብርተኝነት ክስ እንደተመሠረተባቸው የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
ተከሳሾቹ የተጠቀሱባቸው የሕግ አንቀጾች ዋስትና ስለሚከለክሉ በማረሚያ ቤት ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ የቅድመ ክስ መቃወሚያ ካላቸው እንዲያቀርቡና ከጠበቃ ጋር ተመካክረው ታኅሳስ 18 ቀን 2009 ዓ.ም. እንዲቀርቡ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ 

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopian Health Professionals Association Urges Govt to Promptly Respond to Health Workers' Demands Amid Pre-Strike Demonstrations
     Dagmawi Melnilik Hospital, which was later upgraded to a referral hospital, is the nation’s first hospital, built in 1909.Addis Standard (Addis Ababa)As health professionals across Ethiopia stage pre-strike demonstrations demanding improved salaries, benefits, and working conditions, the...
    May-13 - 2025 | More »
  • Commentary: Why Ethiopian university lecturers' strike failed: A cautionary tale for health professionals
     The moment of release of the detained teachers’ coordinators, greeted by fellow teachers awaiting their return. Photo: Provided by the writerIn 2022, Ethiopian university lecturers launched a year-long social media campaign  and subsequent threat for indefinite...
    May-13 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-08 - 2025 | More »
  • ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ
     የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ...
    May-08 - 2025 | More »
  • በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት
     ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ...
    May-05 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-05 - 2025 | More »
  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው  ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara region
     Ethiopian gov’t forces killed 27 civilians in the Amhara regionEthiopian government forces this week reportedly killed 27 civilians, in two separate incidents,  in a latest string of extrajudicial killings in the Amhara region of Ethiopia.  The forces allegedly carried it out in a...
    June-29 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time