Monday, November 7, 2016

የንግድ መደብሮችን የሚተናነቀው የኪራይ ዋጋ

በቻይና የተገነቡ አዳዲስ ከተሞች በተለያዩ ምክንያቶች የሚኖርባቸው እያጡ ፀጥ እረጭ ያሉ ሕይወት አልባ መንደሮች ወደ መሆን እየተቀየሩ መጥተዋል፡፡ በየከተሞቹ የተገነቡት አፓርትመንቶችና የሕዝብ መገልገያ ሕንፃዎች ተዘግተው ውለው ማደር ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ በዚህም ሳቢያ ‹‹ጎሥት ሲቲ›› ወይም የጣረሞት ከተሞች የሚል ቅጽል አትርፈዋል፡፡ እ.ኤ.አ. እስከ 2030 ድረስ 40 በመቶ የሚሆኑት ቻይናውያን ወደ እነዚህ ከተሞች ካልተሸጋሸጉ በስተቀር የሕንፃዎቹ ዕጣ ፈንታ በዚህ መልኩ ሊቀጥል እንደሚችል ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡
በቀላሉ ሊቀረፍ የማይችል የመኖሪያ ቤት ችግር ላለባት ኢትዮጵያ ይህ ዓይነቱ ክስተት መፈጠሩ የማይታሰብ ቢሆንም፣ እየተገነቡ ያሉት ሕንፃዎች ቁጥር ግን በየጊዜው እያሻቀበ ይገኛል፡፡ በአንድ ወቅት በአገሪቱ የዘመናዊነት መገለጫ ሆኖ አንደ ብርቅ ይታይ የነበረ ሕንፃ አሁን ላይ ትልቅ የገቢ ምንጭ እየሆነ ይገኛል፡፡ አዋጭነቱን የተመለከቱ በርካቶች ባለሀብቶችም ሕንፃ በማስገንባት ከኪራዩ ዳጎስ ያለ ገቢ እያገኙ ይገኛሉ፡፡
መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የአገሪቱ የኮንስትራክሽን ዘርፍ በየዓመቱ በ12.43 በመቶ እያደገ ይገኛል፡፡ ለሕንፃ ማስገንቢያ የሚያውሉት ብድር ፍለጋ በአገሪቱ የሚገኙ የፋይናንስ ተቋማትን በሮች የሚያንኳኩም በዝተዋል፡፡ የአንዳንዱ ባንኮች የብድር መዝገብ እንደሚያሳየውም፣ ለአንድ ዓመት ለብድር ተብሎ ከሚያዘው የገንዘብ መጠን ውስጥ እስከ 15 በመቶ ያህሉ ለኮንስትራክሽን በተለይም ለገበያ ማዕከላት ግንባታ እየዋለ ይገኛል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1997 ዓ.ም. እና 1998 ዓ.ም. ከኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ከኪራይ ታክስ የተገኘ ዓመታዊ ገቢ 15.2 ሚሊዮን ብር ነበር፡፡ በ2004 ዓ.ም. እና 2005 ዓ.ም. ግን ይህ መጠን ወደ 78.3 ሚሊዮን ብር ከፍ ሊል ችሏል፡፡ ከዘርፉ የተገኘው ዓመታዊ ገቢም 105 ሚሊዮን ብር እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ከዘርፉ የሚገኘው ዓመታዊ የኪራይ ገቢ የ26.8 በመቶ ዕድገት እንዳለው ይነገርለታል፡፡
ለዚህም ዕድገት ማመሳከሪያ በየመንደሩ የሚገነቡ ሕንፃዎችን ማየቱ በቂ ነው፡፡ ካለው ፍላጎት አንፃር ተገንብተው ያልተጠናቀቁ ሕንፃዎችን ተሽቀዳድመው የሚከራዩ ድርጅቶችና ግለሰቦችን ማየትም ተለምዷል፡፡ በካሬ ሜትር ተመን እየወጣላቸው በመከራየት ላይ የሚገኙት ሁለገብ ሕንፃዎች፣ የሚከራዩበት ዋጋ እንደየአካባቢው የገበያ ሁኔታ እንዲሁም እንደየሕንፃው ወለል ስፋት የተለያየ ነው፡፡
ሕንፃው የተገነባው ከፍተኛ የገበያ ፍሰት ባለባቸው እንደ መርካቶ ባሉ ቦታዎች ከሆነ፣ በካሬ ሜትር እስከ 2,500 ብር ድረስ ይከራያል፡፡ መገናኛ፣ ሲኤምሲ፣ ቦሌ አካባቢ ደግሞ በካሬ ከ400 እስከ 750  ይከራያል፡፡ በከፍተኛ ዋጋ የሚከራዩት በሕንፃው ታችና የመጀመርያው ወለል ላይ የሚገኙ ክፍሎች ሲሆኑ፣ ወደ ላይ ከፍታ በጨመረ ቁጥር ዋጋውም እየቀነሰ ይሄዳል፡፡ አብዛኛዎቹ በተለይም ዓይነተኛ ገበያ ባላቸው አካባቢዎች የሚገነቡ ሕንፃዎች ከመጠናቀቃቸው ወራት ቀደም ብሎ በደንበኞች ይያዛሉ፡፡ በጨረታ አወዳድረው የሚያከራዩም በርካቶች ናቸው፡፡
ይሁን እንጂ የሕንፃዎች ዋጋ ውድ እየሆነ መምጣቱ ተከራዮችን የሚያማርር ሆኗል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜም የሚጠይቁት ዋጋ ጭማሪ አሳሳቢ እየሆነ መጥቷል፡፡ የምሥራች ብርሃን ትባላለች፡፡ መገናኛ አካባቢ በሚገኝ አንድ ሕንፃ ውስጥ ተከራይታ  የመዋቢያ ምርቶችን ትሸጣለች፡፡ ሕንፃው ውስጥ ያሉ ክፍሎች በካሬ ሜትር እስከ 400 ብር ይከራያሉ፡፡ ካላት አቅም አንፃር ግን የምሥራች የተከራየችው ከሕንፃው መወጣጫ ደረጃ ሥር የሚገኘውን ክፍት ቦታ ነው፡፡ በወር 3,000 ብር እንደምትከፍልበት ገልጻለች፡፡
40,000 ብር የሚገመት ዋጋ ያላቸው ዕቃዎችን ደርድራ የምትሸጠውና የምትደረድረው ከመወጣጫው ሥር ባስቀመጠቻቸው ባለመስታወት መደርደሪያዎች ነው፡፡ ሥራዋን ጨርሳ ስትወጣም መደርደሪያዎቹን በቁልፍ መቆለፍ ብቻ እንጂ ንብረቷን ከዘረፋ ለመከላከል የምትዘጋው በር የላትም፡፡ በአንድ ወቅት መደርደሪያዋ ተሰብሮ እንዳገኘችው ገልጻለች፡፡ ሌሎችም ችግሮች አጋጥመዋት ያውቃሉ፡፡ ይሁንና ከዚህ የተሻለ አማራጭ ስለሌላት ቦታውን ትታ ለመሄድ አታስብም፡፡ በዚህ መልኩ ስትሠራ ሁለት ዓመት አስቆጥራለች፡፡ ሕንፃውን ከተከራዩ ሰዎች ውስጥም ከመጀመርያዎቹ መካከል አንዷ ነች፡፡
በካሬ ሜትር ከሚጠየቀው ዋጋ በተጨማሪ በአንድ ጊዜ የበርካታ ወራት ኪራይ እንዲከፍሉ የሚገደዱበት አሠራር ተከራዮችን እያስጨነቀ የሚገኝ ነው፡፡ የተባሉትን መክፈል ካልቻሉም አፍታ ሳይቆዩ ቦታቸውን የሚረከቡ ተፎካካሪዎች በርካቶች ናቸው፡፡ ለዚህም ያላቸውን አሟጥጠው አልያም ተበድረው መክፈል ግድ ይላቸዋል፡፡
 ‹‹የ6 ወር 18,000 ብር ከፍዬ ነው የተከራየሁት፤›› የምትለው የምሥራች፣ አንዳንዴ ከፍተኛ ገንዘብ ከፍለው የተከራዩት ሕንፃ በቶሎ ላይለመድ፣ ገበያ ላይኖረው እንደሚችል፣ ለወራት በኪሳራ መቆየት እንደሚያጋጥም ተናግራለች፡፡
‹‹በመጀመርያዎቹ ወራት አንድ ቻፕስቲክ እንኳ ሳልሸጥ የምውልባቸው ቀናት ይበዙ ነበር፡፡ አሁንም ብዙ ለውጥ የለውም፡፡ ከጊዜ በኋላ ግን የገበያው ሁኔታ ይስተካከላል፡፡ ሲስተካከል ደግሞ በካሬ ሜትር የሚከፈለው ዋጋ አብሮ ይጨምራል፤›› በማለት ጫናው ምን ያህል እንደሆነ አብራርታለች፡፡
 ‹‹አንድ ቦታ ላይ ሆኖ ገበያ ካለማመዱና ደንበኛ ካፈሩ በኋላ ኪራዩ ተወደደ ብሎ ሌላ መቀየር ዋጋ ያስከፍላል፡፡ ከለመዱበት ቦታ መጥፋት  ደንበኞችን ያባርራል፤›› የሚለው የበርካታ ተከራዮች እምነት ነው፡፡ በመሆኑም ጥርሳቸውን ነክሰው የተከራዩትን ቤት ላለመልቀቅ ይጣጣራሉ፡፡
ቦሌ ከሚሊኒየም አዳራሽ አጠገብ በሚገኘው ስናፕ ፕላዛ ሕንፃ ውስጥ ሱቅ የተከራችው ቅድስት ዮሐንስ (ስሟ ተቀይሯል) እንደ የምሥራች ሁሉ በኪራይ ተማርራለች፡፡ ሱቋን የተከራየችው ከቫት በፊት በካሬ ሜትር 350 ብር ከፍላ ነው፡፡ እዚያ ከመግባቷ በፊት ቦሌ መድኃኔዓለም ፊት ለፊት ከሚገኙት ሕንፃዎች መካከል አንደኛውን ተከራይታ ትሠራ ነበር፡፡ ነገር ግን የደረሳት ሱቅ ከሕንፃው የፊት መግቢያ ዞር ያለ ስለነበር የሚከፈልበትን ያህል ገበያ አልነበረውም፡፡ ‹‹ቦሌ አካባቢ ሁሉም ውድ ናቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ሰው አይደፍርም፡፡ ነገር ግን ርካሽ ናቸው ተብለው የሚገመቱ ቦታዎችም ላይ የዕቃ ዋጋ በጣም ይወደዳል፤›› በማለት የገበያውን አዝማሚያ ትገልጻለች፡፡
ሕንፃዎቹ የሚተዳደሩበት የየራሳቸው ደንቦች ሲኖራቸው ቅድስት በተከራየችበት ሕንፃ ያለው አሠራር ጠዋት ሦስት ሰዓት ላይ ሱቆች መከፈት እንዳለባቸው የሚጠይቅ ነው፡፡ ምሽት ሁለት ሰዓት ደግሞ ሱቆች የሚዘጉበት መውጫ ጊዜ ነው፡፡ በተከራዩና በአከራዩ መካከል የኪራይ ዋጋ ጭማሪና የመሳሰሉትን የሚገዛ ስምምነት ይፈጸማል፡፡ አንደኛው ወገን ውል ካፈረሰም በውሉ መሠረት ይጠየቃል፡፡
የማከራየት ሥራው የሚጀምረው ሕንፃዎች ቅርፅ መያዝ እንደ ጀመሩ፣ የማጠናቀቂያ ግንባታቸው ወቅት ላይ ነው፡፡ ይህ በሕንፃ ሕጉ መሠረት የማይፈቀድ አሠራር ቢሆንም ባንኮች፣ የመድን ድርጅቶች ያላለቀ ሕንፃ በመከራየት የሚወዳደራቸው ያለ አይመስሉም፡፡ እንዲህ ባለው ሒደት ግለሰብ ተከራዮች አልፎ አልፎ በጨረታ እንዲወዳደሩ ሲደረግ ይታያል፡፡ ሕንፃው ለአገልግሎት እስኪበቃ ለወራት መጠበቅም የተለመደ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በአሁኑ ወቅት እየተለወጠ ያለ ይመስላል፡፡ በከተማው እንደ አሸን እየፈሉ ካሉት በተለይም በቅርቡ ከተሠሩት ሕንፃዎች መካከል የሚከራያቸው ሳያገኙ ቀርተው አሊያም በሌላ ምክንያት ባዷቸውን ገትረው የሚታዩ አልታጡም፡፡ የገበያ ሁኔታ፣ የኪራይ ዋጋቸው መወደድ እንዲሁም የክፍሎቹ ወለልና ለተለዩ አገልግሎቶች እንዲውሉ የተዘጋጁ ሆነው ለተፈለገው ጉዳይ የሚከራያቸው ደንበኛ አለመገኘት ሊጠቀሱ የሚችሉ ምክንያቶች ናቸው፡፡
በዘፍመሸ ግራንድ ሞል የማርኬቲንግ ባለሙያ ሆነው የሚያገለግሉት አቶ ውብሸት አበራ እንደሚሉት፣ በሕንፃው ውስጥ ከሚገኙ በርካታ ክፍሎች መካከል አሥር ሱቆች እስካሁን አልተከራዩም፡፡ ይህም የሆነው የገበያ ማዕከል የሚለውን ስያሜ ለማሟላት ታስቦ ሱቆቹ ለንግድና ግብይት አገልግሎቶች የታጩ በመሆናቸው እስካሁን በተፈለገው ዘርፍ የተሰማሩ ደንበኞች ሊመጡ ስላልቻሉ ነው፡፡
አንድ ሕንፃ የሚከራይበትን ዋጋ የሚወስኑት ሕንፃው የተገነባበት ቦታ፣ ንጽህናው፣ በቂ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ያካተተ መሆኑና ከስርቆትና ከሌሎች የደኅንነት ሥጋቶች የፀዳ መሆኑ እንደሚጠቀሱ አቶ ውብሸት ይገልጻሉ፡፡
አንድ ሕንፃ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ በኋላ የሚመጡ ሌሎች ተጨማሪ ወጪዎች መኖራቸውን፣ ለመንግሥት ገቢ የሚደረገው ታክስ ከፍተኛ መሆኑን በመጥቀስ በካሬ ሜትር የሚከፈለው የኪራይ ዋጋ የተጋነነ አለመሆኑን የሚከራከሩ የሕንፃ ባለቤቶችም አሉ፡፡ ከሕንፃ ኪራይ በዓመት የሚገኘው ገቢ 7,200 ብር ከሆነ ከግብር ነፃ ነው፡፡ ከ7,201 እስከ 19,800 ባለው የገቢ ልክ የ10 በመቶ ታክስ ይከፈልበታል፡፡ ገቢው ከ19,801 እስከ 38,400 ባለው መጠን ሲወድቅ የ15 በመቶ፣ 38,401 እስከ 63,000 ሲሆን የ20 በመቶ፣ ከ63,001 እስከ 93,600 ሲሆን የ25 በመቶ፣ ከ93,601 እስከ 130,800 ሲሆን፣ የ30 በመቶ እና በዓመት የሚገኘው ገቢ ከ130,800 በላይ ሲሆን ደግሞ የ35 በመቶ የኪራይ ገቢ ግብር እንዲከፈል፣ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ አዋጅ ያስገድዳል፡፡ የ15 በመቶ ተጨማሪ እሴት ታክስ መክፈልም ግዴታ ነው፡፡
ከዚህ ባሻገር ሕንፃዎቹ ከተከራዩ በኋላ ወጣ ገባ የሚሉ ተከራዮች ስለሚበዙ እንደ ቧንቧ፣ የበር ቁልፍ የመሳሰሉት በየጊዜው መቀየር እነዚህንም ተከታትሎ ለማስተካከል ወጪዎችን ማውጣት ግድ ነው፡፡ በሌላ በኩልም ሱቆቹን ለመከራየት የሚፈልጉ ደንበኞች ካላቸው የመክፈል አቅም አኳያ አነስተኛ ቦታ ይፈልጋሉ፡፡ ይህ የአብዛኛዎቹ ተከራዮች ፍላጎት ስለሆነ ነገሩን ቸል ማለት ከገበያ ውጭ ሊያደርግ ስለሚችል፣ ተከራዮች በሚፈልጉትና በአቅማቸው መሠረት የሕንፃ ክፍሎችን በመሸንሸንና በመከፋፈልና ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም በሚሊዮኖች የሚቆጠር ተጨማሪ ገንዘብ እንደሚያወጡ አከራዮች ያብራራሉ፡፡
አቶ አብርሃም ገላው ካዛንቺስ አካባቢ የሚገኝ አንድ ሕንፃ ባለቤት ናቸው፡፡ እሳቸው እንደሚሉት፣ ሕንፃው የተገነባው ከአምስት ዓመት በፊት ነው፡፡ በአንድ ወለል ላይ እስከ 20 የሚደርሱ ሱቆች አከራይተዋል፡፡ በ1,000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈውን ባለ አሥር ፎቅ ሕንፃ የላይኛውን ክፍል የተከራዩት ቢሮዎች ናቸው፡፡
 ‹‹ከሕንፃው ውስጥ የተለያዩ ትንንሽ ዕቃዎች መስረቅ የተለመደ ነው፡፡ የጠፉትን ዕቃዎች ለማሟላትም በየጊዜው ትንሽ የማይባል ገንዘብ ይወጣል፤›› የሚሉት አቶ አብርሃም፣ ሽንሽን ለማዘጋጀት የሚወጣው ገንዘብ ደግሞ የበለጠ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
እንደ እሳቸው ገለጻ፣ አብዛኛዎቹ ደንበኞች ከ20 እስከ 30 ካሬ ስፋት ያለው ቦታ ይፈልጋሉ፡፡ ከ100 እስከ 200 ካሬ የሚጠይቁም አሉ፡፡ ነገር ግን በቁጥር የሚበዙት 20 ካሬ የሚፈልጉት ናቸው፡፡ እነሱ በሚፈልጉት መጠን ከፋፍሎ ለማዘጋጀትም ከአራት ሚሊዮን ብር በላይ ለማውጣት መገደዳቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ይህ የአብዛኞቹ ሕንፃዎች ገጠመኝ ቢሆንም ዋጋው ግነት እንዳለበት የሚናገሩ አካላት ግን አልታጡም፡፡
የሕንፃ ዲዛይን አማካሪው አቶ ዳዊት ታምሩ፣ አንድ ካሬ ሜትር ቦታ ለመገንባት ከ5,000 እስከ 15,000 ብር እንደሚፈጅ፣ 15,000 ብር ወጪ የሚጠይቁት እንደ ሆቴል ያሉ ግንባታዎች መሆናቸውን፣ ለንግድ ማዕከላትና ቢሮዎች ግንባታ የሚወጣው ወጪ ቢበዛ ከ5,000 እስከ 6,000 ብር እንደሚሆን አቶ ዳዊት ገልጸዋል፡፡ አክለውም በሽንሽን ከፋፍሎ ለማዘጋጀት ‹‹በአሉሚኒየም የሚሠራው ውድ ፓርቲሽን ነው፡፡ ለዚህም ቢሆን ግን በካሬ 3,000 ብር ይበቃል፡፡ በፒቪሲ መሥራት ካስፈለገም በካሬ 2,000 ብር በቂ ነው፡፡ በጂፕሰም ከተሠራ ደግሞ በካሬ በ1,000 ብር አይሞላም፤›› ማለትም በአሁኑ ወቅት በካሬ ሜትር እየተጠየቀ ያለው ዋጋ ምክንያታዊ አለመሆኑን ያስረዳሉ፡፡
እንዲህ ዝብርቅርቅ የሆነውን የኪራይ ሥርዓት ለማስተካከል መንግሥት ቸልተኛ ሆኗል፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት የኪራይ ዋጋ ተመንን የሚገዛ ሕግ እንደሚያወጣ ቢያስታውቅም እስካሁን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አይታይም፡፡ የንግድ ቤቶችን የኪራይ ዋጋ አነሳን እንጂ እየናረና የብዙዎችን ኢኮኖሚያዊ ሰብዕና እየተፈታተነ የሚገኘው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋም፣ ‹‹በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ፤›› እንደሚባለው በኑሮ ውድነት ላይ ተጨማሪ ፈተና በመሆን የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን እየተፈታተነ የሚገኝ ችግር ነው፡፡ መንግሥት ለዚህም የኪራይ ተመን እንደሚያወጣ ካስታወቀ ሰነባብቷል፡፡ ይህ ነው የሚባል ውጤት ግን እስካሁን አላመጣም፡፡   Read more here

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopia: 75-Year-Old Civilian Brutally Murdered in Church by Abiy Ahmed Regime’s Forces
     In a shocking and disturbing incident, 75-year-old Mr. Fentaw Derbew, a civilian, was brutally murdered while attending a mass at Kobo Michael Church in Raya Kobo Woreda, North Wollo Zone in Ethiopia. According to eyewitnesses and sources, Mr. Fentaw Derbew was killed by the Abiy Ahmed...
    July-27 - 2025 | More »
  • Ethiopian Health Professionals Association Urges Govt to Promptly Respond to Health Workers' Demands Amid Pre-Strike Demonstrations
     Dagmawi Melnilik Hospital, which was later upgraded to a referral hospital, is the nation’s first hospital, built in 1909.Addis Standard (Addis Ababa)As health professionals across Ethiopia stage pre-strike demonstrations demanding improved salaries, benefits, and working conditions, the...
    May-13 - 2025 | More »
  • Commentary: Why Ethiopian university lecturers' strike failed: A cautionary tale for health professionals
     The moment of release of the detained teachers’ coordinators, greeted by fellow teachers awaiting their return. Photo: Provided by the writerIn 2022, Ethiopian university lecturers launched a year-long social media campaign  and subsequent threat for indefinite...
    May-13 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-08 - 2025 | More »
  • ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ
     የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ...
    May-08 - 2025 | More »
  • በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት
     ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ...
    May-05 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-05 - 2025 | More »
  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው  ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time