Wednesday, November 16, 2016

የአትላንታው የኦሮሞ ተወላጆች ጉባዔ

ፕሮፌሰር ሕዝቅዔል ገቢሣ
ከተለያዩ የሕይወት መስኮች የተሰባሰቡ ከስድስት መቶ በላይ የሚሆኑ የኦሮሞ ተወላጆች በጆርጂያ ግዛት ዋና ከተማ አትላንታ ላይ ያደረጉት ጉባዔ ተጠናቅቆ የሥራ ሠነድ አውጥቷል፡፡
የጉባዔው ዓላማ የተለያዩ ሃሣቦችና አቋሞች ያሏቸው የኦሮሞ ድርጅቶች ኃላፊነት ባለው መንገድ እንዲንቀሣቀሱና በአንድ መድረክ እንዲታገሉ ለማስቻል፣ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ የነቃና ሥፋት ያለው ውይይት ለማካሄድ መሆኑን ከአስተባባሪዎቹ አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ሕዝቅዔል ገቢሣ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡
የሠብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅት እንዲቋቋምም ሃሣብ ቀርቧል፡፡
“የኦሮሞ አብዮት” ሲል የጉባዔው መግለጫ በጠራው እንቅስቃሴ ውስጥ ከሌሎች ነፃነት አፍቃሪ ሕዝቦች ጋርም እጅ ለእጅ ለመያያዝ እንደሚሠሩ ተሣታፊዎቹ አመልክተዋል፡፡
ከፕሮፌሰር ሕዝቅዔል ገቢሣ ጋር ያደረግነውን ሙሉ ቃለ-ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ Read more here

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time