Tuesday, October 11, 2016

“አገሪቱ መስቀለኛ መንገድ ላይ ናት”


* የኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሟል፤አዲስ ሃኪምና መድሃኒት ይፈልጋል
* ኢህአዴግ ውስጥ ካለው ምሁር በተቃዋሚው ጎራ ያለው በእጅጉ ይልቃል
* ኢህአዴግ ለኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ውለታ እንዲውል እጠይቀዋለሁ

    ለ3 ወራት ገደማ አሜሪካ ቆይተው የተመለሱት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ በወቅታዊ አገራዊ ችግሮች ዙሪያ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ
ጋር ቃለምልልስ አድርገዋል፡; በተጨማሪ በአሜሪካ በነበራቸው ቆይታ ምን እንዳከናወኑ፣ የዳያስፖራው ፖለቲካ ምን እንደሚመስልና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል - ዶ/ር መረራ ጉዲና፡፡

እስቲ የአሜሪካ ጉብኝትዎ አላማ ምን እንደነበር በዝርዝር ይንገሩኝ?
በሶስት ምክንያቶች ነበር ወደ አሜሪካ የተጓዝኩት። አንደኛው የዲፕሎማቲክ ስራ ነው። ይሄን ሃገር እንግዲህ ቅኝ እየገዙ ነው የሚባሉት አሜሪካኖች ናቸው፡፡ በማይሆን ግንኙነት እንዳይጎዱን፤ በኢትዮጵያ ላይ ያለውን ፖሊሲ እንዲመረምሩ፤ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል እንዲያግዙ…ወዘተ መጠየቅ አንዱ አላማ ነበር፡፡ በሁለተኛነት፣በአሜሪካ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና የኦሮሞ ማህበረሰብ ጋር ለመወያየት ነው፡፡ በሶስተኝነት፣ ለድርጅታችን ድጋፍ ለማሰባሰብ ነው። 
ከአሜሪካ ባለስልጣናትም ጋር ተገናኝተዋል፡፡  ውይይታችሁ በምን ላይ ያተኮረ ነበር?
የሃገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ በሚመለከት የሴኔት አባላት፣ በተለይ የህግ ጉዳዮችን ከሚያዘጋጁት ጋር ተነጋግሬያለሁ፡፡ ከ‹‹ሠማያዊ›› ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ይልቃል ጌትነት ጋር ‹‹አትላንቲክ ካውንስል›› ከሚባል የአሜሪካ የሃሣብ አመንጭዎች ቡድን ጋር ተወያይተናል፡፡ እዚያ ውስጥ ከነበሩትና አስቀድሞ ከማውቃቸው መካከል፣ በ1983 ለንደን ላይ ኢህአዴግ ሃገር እንዲረከብ፣ ምርቃት የሰጠው፣ ሄርማን ኮኽ የሚባለው ሰው ነበር፡፡ የቀድሞ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ዴቪድ ሺል የሚባለውም ነበር፡፡ እንዲሁም ከሌሎች የአሜሪካ ባለ ራዕዮችና ሃሳብ አመንጪዎች ጋር 2 ሰዓት የፈጀ ውይይት አድርገናል፡፡ በአብዛኛውም አሁን በሃገሪቱ ባሉ የህዝብ ተቃውሞዎች ላይ አተኩረን ነው የተወያየነው፡፡
በሃገሪቱ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ምን አስተያየት አላቸው? የተሟላ መረጃስ ያገኛሉ?
እነሱ ሁሉንም ያወቃሉ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታና የሚደረገውን ነገር በተመለከተ በቂ መረጃ አላቸው፡፡ የራሳቸው መንግስት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲም ችግር እንዳለው ያውቃሉ፡፡  በተደጋጋሚ፣‹‹ተቃዋሚው አንድ ሆኖ አልወጣም፤ አንድ ላይ ሆናችሁ ለማየት እንፈልጋለን›› የሚል ሀሳብ ነበር የሚሰነዝሩት፡፡ 
ከዳያስፖራው ማህበረሰብ ጋር ያደረጋችሁት ውይይትስ----ምን ይመስላል?
ስለ ዳያስፖራው ፖለቲካ፣በመፅሐፌ ላይ ገልጬዋለሁ፡፡ ዳያስፖራው እንደ ማናችንም በሃገር ጉዳይ የሚጨነቅ ነው፡፡ ክፍፍሉ እዚህም እንዳለው፣ እዚያም ይንፀባረቃል፡፡ ምናልባት እዚህ ካለው ጎልቶ ይታይ ይሆናል፡፡ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ የማክረር ዝንባሌ ይታያል፡፡ ጎንደር ላይ በተደረገው ሰልፍ፣ህዝቡ የኦሮሞን ህዝብ ደግፎ እንደሚቆም ከገለጸ በኋላ፣ በዳያስፖራው ዘንድ ቀድሞ የነበረውን አመለካከት የቀየረው ይመስላል፡፡ በአገር ውስጥ የተፈጠረው አንድነት፣ የዳያስፖራውን ክፍፍል ማስቀረት ብቻ ሳይሆን አዲስ አይነት ግንኙነት እንዲጀመርም አድርጓል፡፡ አንድ ላይ ሠላማዊ ሠልፍ የመውጣት፤ በጋራ የመሠብሠብ ነገር መፈጠሩን ለማየት ችያለሁ፡፡ አሁን በዳያስፖራው የእርስ በእርስ ግንኙነት ላይ ለውጥ አለ ብዬ መናገር እችላለሁ፡፡  
በሃገር ውስጥ ያለው ተቃውሞና ግጭት የተለያየ መልክና ቅርፅ እየያዘ ወደ አንድ አመት ገደማ ሊያስቆጥር ነው፡፡ ተቃውሞው ከቀጠለ ሁኔታዎች ወዴት የሚያመራ ይመስልዎታል?
እኔ ደጋግሜ እንደምለው፣ ሃገሪቱ አሁን መስቀለኛ መንገድ ላይ ናት፡፡ የኢህአዴግ መሪዎች ልቦና ገዝተው፣ ሃገሪቷንና ህዝቦቿን ወደተሻለ የጋራ የፖለቲካ ስርአት… ማለትም መነጋገርና መደራደር ወደሚቻልበት መስመር ካልገቡ፣ ቻይኖች፤ ‹‹ቀውስ የተሻለ ሁኔታን ይዞ ይመጣል›› እንደሚሉት፣ያ እድል ሊመጣ ይችላል፡፡ ወደ እርስ በእርስ ግጭት ሊያመራ የሚችልበት ዕድልም አለ፡፡  
መንግስት ችግሮች ለመፍታት ጥልቅ ተሃድሶ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጿል፡፡ ከዚህ በተረፈ የሚፈጠሩ ሁከቶች ተቀባይነት እንደማይኖራቸው ጠቁሞ፣በሃይል እርምጃ ህግና ስርዓት አስከብራለሁ ብሏል፡፡ ከእነዚህ የመፍትሄ መንገዶች ምን ውጤት ይጠብቃሉ?
ተሃድሶና የሃይል እርምጃ ከዚህ በፊትም ውጤት እንዳላመጡ ታይቷል፡፡ እኛ ከዚህ ቀደም መሬት ዘረፋን በሚመለከት፣በተለይ ማስተር ፕላን ብለው ባወጡት ጉዳይ ላይ መንግስትን ለመምከር ሞክረን ነበር፤አልሠሙንም፡፡ እንደፈራነውም ችግር ተፈጠረ፡፡ ከዚያ በኋላም በየደረጃው እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ ችግሮችን በሠላማዊ መንገድ እንዲፈቱ፤ መንግስት ያልተመጣጠነ ሃይል መጠቀሙ መፍትሄ እንደማይሆን ተናግረናል። ህዝብ ለውጥ እየፈለገ ነው፤መሠረታዊ ለውጥ ነው የሚያስፈልገው፤ እርምጃዎች ውሰዱ ብለን በተደጋጋሚ ወትውተናል፡፡ ነገር ግን ሃሳባችን ቸል በመባሉ የበለጠ ቀውስና ደም መፋሰስ ተከስቷል። አሁንም ቢሆን በፖሊሲዎቻቸው ላይ ደጋግመው ካላሰቡና ወሳኝ እርምጃዎችን ካልወሰዱ አሳሳቢ ነው፡፡ ተሃድሶ የሚባለው ጨዋታ ነው፡፡ ኢህአዴግ ችግር በገጠመው ቁጥር  ተሃድሶ ይላል፡፡ ውጤቱ ግን ጉልቻ መቀያየር ነው የሚሆነው፡፡ ፊት ያለውን ባለስልጣን ወደ ኋላ ወስደው፣ ኋላ የነበረውን ወደፊት ያመጣሉ፤በቃ የእነሡ ተሃድሶ ይሄው ነው። አዲስ ፖሊሲ፣ አዲስ አስተሳሰብ የላቸውም። በተለይ ዲሞክራሲያዊ አሰራር አልታየም፡፡ በኔ እምነት፣ ከዚህ በኋላ ምንም የቀራቸው የሚታደስ ነገር የለም፡፡ ህዝብም ተሃድሶ አይደለም እየጠየቀ ያለው፤ መሠረታዊ ለውጥን ነው፡፡ 
በብዙዎች ዘንድ ኢህአዴግ ስልጣን ቢለቅ፣ሃገርን ተረክቦ ማስተዳደር የሚችል ሃይል የለም የሚል ስጋት አለ፡፡ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው? ስጋቱስ ከምን የመነጨ ነው ይላሉ?
በዋናነት መሰረታዊ ችግሩን የሚፈጥረው ኢህአዴግ ነው፡፡ እንዲህ ያሉ ተቃዋሚዎች እንዳይፈጠሩ ትንሽ ብቅ የሚሉትን እጅና እግራቸውን አስሮ፤ ቢሮ እንዳይከፍቱ እየከለከለና እንዳይንቀሳቀሱ እያደረገ ያለው ኢህአዴግ ነው፡፡ ለዚህ ተጠያቂ መሆን ያለበትም ተቃዋሚው ሳይሆን ኢህአዴግ ነው፡፡ ህገ መንግስቱ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን በተግባር ላይ አላዋለም፡፡ ህገ መንግስቱ፣ነፃ ሚዲያ ይላል፤ ይሄ በተግባር የለም፡፡ ነፃ የዲሞክራሲ ተቋማትን ህገመንግስቱ ይፈቅዳል፤ በተግባር ግን የሉም፡፡ ተቃዋሚም በሚፈለገው ደረጃ እንዳይወጣ አድርጎ የፖለቲካ ምህዳሩን ያበላሸው ኢህአዴግ ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ሽብርተኛ ተብለው ይታሠራሉ፡፡ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ተቃዋሚ ጠንክሮ እንዳይወጣ ሆኗል። ከ97 በኋላ በርካታ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንዴት እንደተፈለጡና እንደተቆረጡ ከማንም የተሠወረ አይደለም፡፡ በአንድ በኩል ይሄን እያደረገ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹እኔ ከሌለው ሃገሪቱ አትኖርም›› እያለ ፕሮፓጋንዳ ያሠራጫል፡፡ አንድ ነገር ግን በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ፡፡ ኢህአዴግ ውስጥ ካለው ምሁር በተቃዋሚው ጎራ ያለው በእጅጉ ይልቃል፡፡ ይሄ በገሃድ የሚታይ ሃቅ ነው፡፡
በልምድም በእውቀትም ኢህአዴግ ውስጥ ካሉት ሰዎች በተቃዋሚ ደጋፊነት ያሉት ይልቃሉ። ስለዚህ አንዳንዶች እንደሚሉት፤እኔ በዚህ በኩል ስጋት የለኝም፤ በርካታ ይህቺን ሀገር ለማስተዳደር የሚመጥኑ ሰዎች አሉ፡፡ ተቃዋሚው ምሁራንን አስተባብሮ ለመምራት ሰፊ አቅምና ተቀባይነት አለው፡፡ ስለዚህ ጭንቀቱ በዋናነት የኢህአዴግ ነው፡፡ “እኔ ከሌለው ሀገር ይፈርሳል፣ መአት ይወርዳል›› እያለ የሚያስወራው ኢህአዴግ ነው፤ ስጋቱም የኢህአዴግ ነው፡፡ በእውቀትም በልምድም ብዙ ምሁራን የመስራት እድል አላገኙም፡፡ ስንት ኢኮኖሚስቶች ናቸው ያሉት? ተቃዋሚው ጋ ስንመጣ፣ በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጭምር የሚያስተምሩ፣ አለም ያከበራቸውና እውቅና የሰጣቸው ሰዎች አሉ፡፡ ስንት ፖለቲካል ሳይንቲስቶች ናቸው ከኢህአዴግ ጋር የሚሰሩት? በአጠቃላይ ሀገሪቷን መምራት የሚችል በእውቀትና በልምድ የዳበረ የሰው ኃይል ያለው በተቃዋሚው ወገን ነው፡፡ ተቃዋሚው እድሉን ቢያገኝ፣እነዚህን የእውቀት ሀብቶች በአግባቡ ተጠቅሞ ሀገሪቱን ይታደጋት ነበር፡፡ 
አሁን በአገሪቱ ለተከሰቱት ቀውሶች መፍትሄው ምንድን ነው ይላሉ?
እኔ ኢህአዴግ አንድ ውለታ እንዲውል የምጠይቀው፣ ብሄራዊ የአንድነት መንግስት እንዲቋቋም እድል እንዲፈጥር ነው፡፡ የፖለቲካ ምህዳሩን ከፍቶ፣ ጉዳዩ ያገባናል ከሚሉ እውነተኛ የህዝብ ተወካዮች ጋር ውይይት መጀመር አለበት። ‹‹ታድሻለሁ›› ብሎ ተቀባብቶ መቅረብ የትም አያደርስም፡፡ መሰረታዊ የሆነ የፖሊሲ፣ የአሰራርና የአመራር ለውጥ ያስፈልጋል፡፡ አንድ መድኀኒት አልሰራም ካለ፣ ሀኪም ያንኑ መድኃኒት መልሶ አያዝም፤ መድኃኒቱን ይቀይራል፡፡ የኢህአዴግም ተሃድሶ ተደጋግሞ ታይቶ፣ ተፈትኗል፤ የመጣ ለውጥ የለም፡፡ ተፈትኖ የወደቀ መድኃኒትን በህዝብ ላይ ደጋግሞ መሞከር ለውጥ አያመጣም፡፡ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሟል፡፡ ለህመሙ አዲስ ሃኪምና መድኃኒት ያስፈልገዋል፡፡ የሚለዋወጡት ሹመኞች እኮ ከካድሬ ትምህርት ያለፈ እውቀት የሌላቸው፣ ተቀባብተው የሚቀርቡ ሰዎች ናቸው፡፡ 
‹‹የብሄራዊ አንድነት መንግስት›› ይቋቋም ሲሉ፣ ይሄን ማን ነው ኃላፊነት ወስዶ ማስተባበር የሚችለው?
ሁሉም አካል አስተዋፅኦ ሊያደርግ ይችላል። ነገር ግን ስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ፣ ከስልጣን እስካልወረደና የደህንነትና ሌሎች ኃይሎችን እስከተቆጣጠረ ድረስ ለዚህ ሃሳብ መንገድ መክፈት ያለበት እሱ ነው፡፡  ይሄ ካልሆነ አስቸጋሪ ነው። ለዚህ ነው ኢህአዴግ ለኢትዮጵያ ህዝብ በዚህ መልኩ ውለታ ይዋል ያልኩት፡፡ አፈና ከሌለ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣ ታዋቂ ሰዎች ወደፊት ለመውጣትና የሂደቱ አካል ለመሆን አይቸገሩም፡፡  
በኦሮሞ የኢሬቻ በአል ላይ በደረሰው አስከፊ እልቂት፣ መንግስትና ተቃዋሚዎች በመንስኤውና  በሞቱ ሰዎች ቁጥር ዙሪያ እየተወዛገቡ ነው፡፡ ህዝቡ ሃቁን እንዲያውቅ ምን መደረግ አለበት?
ይሄ ግልፅ ነው፡፡ ገለልተኛ አካል ጉዳዩን መመርመር አለበት፡፡ የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ ኢትዮጵያውያን ያሉበት አካል፣ጉዳዩን እንዲያጣራ እንፈልጋለን፡፡ የሟቾችን ቁጥር መደበቅ ምንም የፖለቲካ ትርፍ አያመጣም፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ በተሰበሰበበት አስለቃሽ ጭስ ከተለቀቀና ሰዎቹ ታፍነው ጉዳት እንዲደርስ ከተደረገ በኋላ፣ ‹‹የለም እኔ ጥይት አልተኮስኩም›› ማለት አያዋጣም፡፡ ወጣቶቹ በወቅቱ ከተቃውሞ ጩኸት በላይ ያደረጉት ነገር የለም፡፡ በጥፊ እንኳ የተመታ የመንግስት ባለስልጣን የለም፡፡ ገና ለገና የሆነ ነገር ይፈጠራል በሚል ነው እርምጃው የተወሰደው፡፡ ለመቃወም ፈቃድ አያስፈልገውም። ሰዎች ለምን ተቃወሙ አይባልም፡፡ እስከ 3፡30 ሁሉም ነገር በሰላም ይከናወን ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ከመንግስት ጋር የተለየ ግንኙነት አላቸው ተብለው የሚታሰቡ የቀድሞ አባ ገዳን አምጥተው ንግግር እንዲያደርግ ማድረጋቸው አግባብ አልነበረም፡፡ ሌላው ህዝብ መተላለፊያ እንደሌለው እየታወቀ፣ ከባድ ድምፅ የሚያወጣ ጭስ መተኮስ ምን ማለት ነው? ባለስልጣን ባልተነካበት፣ የመንግስትና የህዝብ ንብረት ባልወደመበት… ለምን ጭስም ሆነ የፕላስቲክ ጥይት ይተኮሳል? ይሄ አሳዛኝ ነው፡፡ 
መንግስት በደረሰው አደጋ ማዘኑን ገልፆ፤የ3 ቀን ብሄራዊ የሃዘን ቀን አውጇል …. 
እኔ ይሄን እንደ ፌዝ ነው የቆጠርኩት፡፡ ከዚያ በኋላም ሰላማዊ ሰልፈኞች ተገድለዋል፡፡ ሰሞኑን በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ፍጥጫዎች ነበሩ። ከልብ ቢታዘን ኖሮ፣ ህዝቡን ይቅርታ ጠይቆ፣ ‹‹ከዚህ በኋላ አይደገምም፤የፀጥታ ኃይሉ የወሰደው እርምጃ ትክክል አይደለም›› ተብሎ ይነገራል። ከዚያ ይልቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ለፀጥታ ኃይሉ ምስጋና ነው ያቀረቡት፡፡ ሃዘኔታው ከልብ መሆኑ የሚያጠራጥረው እዚያ ላይ ነው፡፡  Read more here

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

  • Ethiopia: 75-Year-Old Civilian Brutally Murdered in Church by Abiy Ahmed Regime’s Forces
     In a shocking and disturbing incident, 75-year-old Mr. Fentaw Derbew, a civilian, was brutally murdered while attending a mass at Kobo Michael Church in Raya Kobo Woreda, North Wollo Zone in Ethiopia. According to eyewitnesses and sources, Mr. Fentaw Derbew was killed by the Abiy Ahmed...
    July-27 - 2025 | More »
  • Ethiopian Health Professionals Association Urges Govt to Promptly Respond to Health Workers' Demands Amid Pre-Strike Demonstrations
     Dagmawi Melnilik Hospital, which was later upgraded to a referral hospital, is the nation’s first hospital, built in 1909.Addis Standard (Addis Ababa)As health professionals across Ethiopia stage pre-strike demonstrations demanding improved salaries, benefits, and working conditions, the...
    May-13 - 2025 | More »
  • Commentary: Why Ethiopian university lecturers' strike failed: A cautionary tale for health professionals
     The moment of release of the detained teachers’ coordinators, greeted by fellow teachers awaiting their return. Photo: Provided by the writerIn 2022, Ethiopian university lecturers launched a year-long social media campaign  and subsequent threat for indefinite...
    May-13 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-08 - 2025 | More »
  • ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ
     የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ...
    May-08 - 2025 | More »
  • በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት
     ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ...
    May-05 - 2025 | More »
  • ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ
     መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ...
    May-05 - 2025 | More »
  • Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?
     Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in...
    Apr-28 - 2025 | More »
  • በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!
     በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እየተመረተ ነው!ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቀን ከ14 ሺህ ቶን በላይ የዓሣ ምርት የሚገኝበት አቅም መፈጠሩን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ገለጹ። ኢትዮጵያ እምቅ የዓሣ ሀብት ቢኖራትም በተለያዩ ተግዳሮቶች ምክንያት በዘርፉ ተጠቃሚ ሳትሆን መቆየቷን በግብርና ሚኒስቴር ዓሣ ሀብት ልማት ዴስክ ሃላፊ ዶክተር ፋሲል ዳዊት ተናግረዋል። በሀገር ደረጃ...
    Mar-26 - 2025 | More »
  • የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!
     የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ደፋር ማሻሻያዎችን እና አፍሪካን የሚመሩ መፍትሄዎችን ከፒአርሲ ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ አሳሰቡ!የመጀመርያው የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) እና አዲስ የተሾሙት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አመራር አባላት ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂደዋል። ስብሰባውን በኤች.ኢ. ማህሙድ አሊ የሱፍ፣ የAUC ሊቀመንበር እና ኤች.ኢ. በአፍሪካ ህብረት የአንጎላ ሪፐብሊክ ቋሚ ተወካይ እና የፒአርሲ ሊቀመንበር አምባሳደር ፕሮፌሰር ሚጌል ሴሳር...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • ፀሐይ ባለበት የቫይታሚን D እጥረት ለምን?
     ለሰውነታችን ጠቃሚ የሆነው ቫይታሚን ዲ የሚገኘው በፀሐይ ጨረር አማካኝነት በተፈጥሮ ሂደት ነው። ኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት የምታገኝ ሀገር ብትሆንም በቅርቡ የወጣ መረጃ ብዙዎች የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባቸው  ያመለክታል። ለምን ይሆን?ቫይታሚን ዲየቫይታሚን ዲ እጥረት በመላው ዓለም ሰዎች ላይ ስለሚታይ አሳሳቢ መሆኑ ይነገራል። በተለይ በዓመት ውስጥ የፀሐይ ብርሃንም ሆነ ሙቀቷን በውስን ወራት ብቻ በሚያገኙ የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • "እንደ አሮጌ ምንጣፍ የተጣለ" - የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የቪኦኤ በጀት እንዲቋረጥ መወሰኑን አወደሰ!
     የቻይና መንግሥት ጋዜጣ የአሜሪካው ፕሬዝንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) በጀት እንዲቋረጥ መወሰናቸውን አወደሰ።የአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) እና ራድዮ ፍሪ እስያ (አርኤፍኤ) በቻይና መንግሥት ዙሪያ ለዓመታት ሲዘግቡ የቆዩ ሲሆን ትራምፕ የጣቢያዎቹ በጀት እንዲቀነስ ወስነዋል።ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው አርብ ነው። 1300 የቪኦኤ ሠራተኞች በግዴታ እረፍት እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።ተቺዎች ውሳኔው ዲሞክራሲን ወደኋላ የሚጎትት ነው ቢሉም ግሎባል ታይምስ...
    Mar-18 - 2025 | More »
  • Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!
     Killings, abductions, funding shortfalls stifle WFP relief efforts across Ethiopia!Eight personnel dead as org. takes USD 30mln loan to sustain operationsThe World Food Program says security concerns are straining its ability to deliver crucial aid assistance in Ethiopia as no less than eight...
    Sept-15 - 2024 | More »
  • Ethiopia : Dialogue Commission wants gov’t to create “enabling condition
     Professor Mesfin Araya, Chief of the Dialogue Commission (Photo credit : DW Amharic)The National Dialogue Commission on Thursday presented its performance report to the parliament. Unusual about it was that this meeting took place in a hotel, not at the parliament building. The practice...
    June-30 - 2024 | More »
  • Struggles of High-Rise Living
     Located on the western outskirts of AddisAbaba, the Asko 40/60 condominium towers stand tall, promising a modern lifestyle but delivering a daily ordeal for its residents. Among them is Melat Kasa, a pregnant mother of two young children aged 4 and 6, who lives on the 13th floor. “I’ve been...
    June-30 - 2024 | More »
  • TPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessing
     NewsTPLF regains political legitimacy with Justice Ministry’s blessingThe Ministry of Justice has granted the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) the green light to register with the National Election Board of Ethiopia (NEBE) as a political party.Heads of the NEBE were informed of the...
    June-29 - 2024 | More »
  • A father who lost 2 sons in a Boeing Max crash waits to hear if the US will prosecute the company
     Ike Riffel fears that instead of putting Boeing on trial, the government will offer the company another shot at corporate probationPhoto by: Jim Young/APProtesters hold photographs of victims of the 2019 Boeing Ethiopian Airlines crash, including Melvin Riffel, left.By: AP via Scripps...
    June-29 - 2024 | More »
  • Ethiopia’s dam fills threaten Egypt’s lifeline: Calls for international intervention
     Adel Sadawi, a member of the Egyptian Council for Foreign Affairs and former Dean of the Institute for Research and Strategic Studies on Nile Basin Countries, commented on Ethiopia’s announcement of its readiness to carry out the fifth filling of the Grand Ethiopian Renaissance...
    June-29 - 2024 | More »
  • Fashion event brings Kanu, others to Ethiopia
     Former Nigerian national football team striker Nwankwo Kanu and other African former football players are in Addis Ababa to participate in the Shenen Africa Fashion Festival Week 2024Upon arrival at the Addis Ababa Bole International Airport, on Thursday Kanu was welcomed by Ethiopia’s...
    June-29 - 2024 | More »
  • Economic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State Department
     NewsEconomic, conflict spurring human trafficking in Ethiopia: US State DepartmentYemeni Houthis forcing Ethiopian migrants into military serviceThe US Department of State commends the Ethiopian government’s efforts to combat human trafficking but urges that more needs to be done to eliminate...
    June-29 - 2024 | More »

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time