Thursday, May 8, 2025

ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ

 


መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።

ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።

ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።

ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።

በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።

ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።

"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ ሳይሞላ ጀልባው ይዋዥቅ ጀመረ። የየመን ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች በአረብኛ ማውራት ጀመሩ። ስደተኞችን ከጀልባው ለመወርወር ነበር የሚመካከሩት። ከዚያም ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አስገድደው ወደ ባሕሩ ጣሏቸው" ሲል ያስታውሳል።

መንገዱ አደገኛ ቢሆንም በየዓመቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች በዚህ መንገድ ይጓዛሉ።

ሚክስድ ማይግሬሽን ሴንተር እንደሚለው በየዓመቱ ከአፍሪካ ወደ የመን የሚገቡ ሰዎች 100 ሺህ ይደርሳሉ።

ስደተኞቹ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ናቸው። እንደ ሶማሊያ እና ጂቡቲ ካሉ የተቀሩት የምሥራቅ አፍሪካ አገራትም ዜጎች ይሰደዳሉ።

መሐመድ በተጓዘበት ጀልባ 47 ኢትዮጵያውያን፣ 5 ሶማሌያውየን እና 2 የየመን ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ነበሩ።

"በጣም አስጨናቂ ነበር። ውሃ ወደ ጀልባው ይገባል። ውሃውን ለማስወጣት ስንሞክር ነበር። በሕይወት መትረፋችንን እርግጠኛ አልነበርንም" ይላል።

ከአውሮፓውያኑ 2014 ጀምሮ የመን በእርስ በርስ ጦርነት እየተናጠች ነው። ስደተኞች ወደ ሳዑዲ አረቢያ መግባት ነው የሚፈልጉት። በሳዑዲ የሚፈለጉ ሠራተኞች ቁጥር ከፍተኛ ነው።

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም (አይኦኤም) እንደሚለው፣ አብዛኞቹ ስደተኞች ጥያቄያቸው የኢኮኖሚ ቢሆንም በተለይ ከአማራ ክልል እና ከኦሮሚያ ክልሎች የሚሰደዱት ወጣቶች ግጭት እና እስራትን በመሸሽ ነው ከኢትዮጵያ የሚወጡት።

'ምሥራቃዊው መንገድ'

ሕገ ወጥ ስደተኞቹ ጂቡቲ በሚገኘው ኦቦክ በኩል አድርገው ደቡብ ምዕራብ የመን ወደሚገኘው ላሂጅ ይገባሉ።

ከሶማሊያ ቦሳሶ የሚነሱት ስደተኞች ደግሞ በየመን ደቡብ ምሥራቅ በሚገኘው ሻብዋህ የባሕር ዳርቻ ይደርሳሉ።

መሐመድ በሁለቱም መንገድ ተጉዟል። ከጂቡቲ ላሂጅ ለመድረስ አምስት ሰዓታት ወስዶበታል።

በአውሮፓውያኑ 2014 ወደ ሶማሊያ ከተመለሰ በኋላ በሶማሊያዋ ቦሳሶ በኩል ወደ የመን ገብቷል።

"በሁለተኛው ጉዞ አልፈራሁም። የመጀመሪያው ከጂቡቲ ያደረግኩት ጉዞ ረዥም ነበር። የመን ለመግባት 24 ሰዓት ወስዶብናል" ይላል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም እንደሚለው፣ ወደ የመን ለመሄድ ዋነኛው መንገድ ጂቡቲ ነው።

በአውሮፓውያኑ 2023 ብቻ 106 ሺህ ኢትዮጵያውያን ጂቡቲ ገብተዋል። ከአገራቸው ተነስተው የጂቡቲ ድንበር ለመድረስ ሳምንታት ይጓዛሉ።

ከአማራ ክልል የሚነሱ ስደተኞች ኦቦክ ለመድረስ 400 ኪሎሜትር ይጓዛሉ።

በመኪና፣ በአውቶብስ ወይም በእግር ነው ጉዞውን የሚያደርጉት። በጋ ላይ ሙቀቱ እስከ 50 ሴንቲግሬድ ይደርሳል።

ባሕር ዳርቻ ላይ ለሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች 300 ዶላር ከፍለው የኤደን ባሕረ ሰላጤን ለመሻገር ይሞክራሉ።

የሚክስድ ማይግሬሽን ሴንተር ቀጣናዊ ዳይሬክተር አይላ ቦንፊግሎ እንደሚሉት፣ ሕገ ወጥ የሰው ዝውውር ብዙዎች የተሰማሩበት ንግድ ነው።

"100 ሺህ ስደተኞች 300 ዶላር ቢከፍሉ 30 ሚሊዮን ዶላር የሚገኝበት ሥራ ነው ማለት ነው" ይላሉ።

በየመን የተዋቀረ መንግሥት አለመኖሩ ለሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም እንደሚለው፣ ባለፉት 10 ዓመታት ውስጥ 1,400 ስደተኞች በጉዞ ላይ ሳሉ ባሕር ውስጥ ሰጥመው ሞተዋል።

አይላ በበኩላቸው ቁጥሩ ከዚህም እንደሚበልጥ ይገምታሉ።

"ይህ ምሥራቃዊው የስደተኞች መንገድ በአህጉሪቱ በጣም አደገኛው ነው። በሕገ ወጥ መንገድ ባሕር ሲያቋርጡ የሚጠቀሙት የተበላሹ ጀልባዎች ነው" በማለት ለሚደርሰው አደጋ አንዱን ምክንያት ጥጠቅሳሉ።

ምን ያህል ስደተኞች እንደሞቱ በትክክል እንደማይታወቅ ያስረዳሉ።

ስደተኞች መንገድ ላይ ከሚገጥማቸው ፈተና ባሻገር በሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ብዝበዛም ይደርስባቸዋል።

"አምና 350 ስደተኞች አነጋግረን ነበር። ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ስለ ጉዞው የተዛባ መረጃ ሰጥተው እንዳሳሳቷቸው ይናገራሉ" ይላሉ አይላ።

"ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎቹ ናቸው ለብዝበዛ የሚያጋልጧቸው። አካላዊ ጥቃት፣ ዝርፊያ እና ስቃይ ይደርስባቸዋል" ሲሉም ዳይሬክተሯ ያክላሉ።

አፍሪካውያን ስደተኞች ባሕሩን ከተሸገሩ በኋላም በሚደርሱባቸው አገራትም ለብዝበዛ ይጋለጣሉ።

በግጭት የምትናጠውን የመን ካለፉ በኋላ ሳዑዲ አረቢያ ቢገቡም ብዝበዛው ይቀጥላል።

"ጦርነቱ ጉዟችንን የበለጠ ከባድ አድርጎታል" ይላል መሐመድ።

ከየመን ሳዑዲ ለ11 ቀናት በእግር መጓዛቸውን ያስታውሳል። ያለ በቂ ምግብ እና ውሃ ነበር ድንበር የተሻገሩት።

"አንድ አብራን ትጓዝ የነበረች ሴት በረሃብ እና በውሃ ጥም ሞታለች" ይላል።

ሳዑዲም ስደተኞች ድንበሯን አቋርጠው እንዳይገቡ ትከላከላለች።

ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው" የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች እሮሮ እና ጥያቄ

 የደሞዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያነሱ የጤና ባለሙያዎች መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ ተናገሩ።

ባለሙያዎቹ ጥያቄዎቻቸውን ለመንግሥት ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፤ ምላሽ እንዲሰጣቸውም የ30 ቀናት ቀነ ገደብ ከሰጡ ሳምንታት ተቆጥረዋል።



የጤና ባለሙያዎቹ "መኖር አቅቶናል" ያሉ ሲሆን፤ በተለያዩ መንገዶች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።

ሐኪም ለመሆን 23 ዓመታትን በትምህርት እንዳሳለፉ ለቢቢሲ የተናገሩት ዶ/ር ይማም እንድሪስ ጠቅላላ ሐኪም ሲሆኑ፤ በቅርቡ የማኅበራዊ የትስስር ገፅ አነጋጋሪ የሆነ የኑሮ ሁኔታቸውን የሚያሳይ መልዕክት ከምስሎች ጋር አጋርተዋል።

"ቤተሰቤ ብዙ [ገንዘብ] እንደማገኝ [ያስባሉ]፤ ሐኪም ልጅ ስላላቸው የሚኮሩ ናቸው" የሚሉት ዶ/ር ይማም፤ ለቤተሰባቸው ችግር አለመድረሳቸው ልባቸውን እንደሰበረው ተናግረዋል።

"23 ዓመት መስዋዕትነት ለከፈለልኝ ቤተሰብ በወር አንድ ኪሎ ቡና መሸፈን የማልችል ሐኪም ነው የሆንኩት። በጣም ነው የሚሰማው" ይላሉ።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ በአዲስ አበባ የሚሰሩ የጤና ባለሙያ በበኩላቸው "መብላት አልቻልንም፤ ልጆቻችንን ማስተማር አልቻልንም፤ ቤት ኪራይ መክፈል አልቻልንም" ሲሉ ጥያቄያቸው የሚያድር እንዳልሆነ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

"መጀመሪያ ባለሙያው ጤነኛ መሆን አለበት እኮ ሌላ ሰው ለማከም። እርሱ በአካል፤ በአእምሮ ጤነኛ መሆን አለበት። አሁን ያለው ባለሙያ እንደዛ [ጤነኛ] አይደለም" የሚሉት ዶ/ር ይማም፤ "አብዛኛው ሐኪም በሕይወቱ ደስተኛ አይደለም። በማማረር፤ ጠዋት ቁርስ በልቶ ስለሚበላው ምሳ የሚያስብ ሐኪም ነው ያለው" ብለዋል።

"እኔ ነኝ ለእነርሱ [ለቤተሰቦቼ] መሆን ያልቻልኩት። . . . ሐኪም በመሆኔ ያተረፍኩት ድኅነትን ነው። ሰው ሰርቶ ሲቀየር አይተናል። ነገ የተሻለ ቀን ይመጣል በሚል ነው [የቆየነው]" ሲሉም አክለዋል።

ዶ/ር ይማም በዚህ ምክንያት የጤና ባለሞያዎች ሙያውን ጥለው እየወጡ እና እየተሰደዱ እንደሆነም ተናግረዋል።

ስፔሻሊት ሐኪም የሆኑት ዶ/ር ማህሌት ጉዑሽ መንግሥት ለጤና ባለሞያዎች ያለው እይታ እና አያያዝ ወደ ሌላ አገር ተሰድደው እንዲሰሩ እንደገፋፋቸው ይናገራሉ።

በተሻለ ክፍያ እና አያያዝ ሶማሌላንድ ሰርተው እንደተመለሱ የተናገሩት ዶ/ር ማህሌት፤ መኖር የሚያስችል ክፍያ ይከፈለን ሲሉ ይጠይቃሉ።

"የሥነ አዕምሮ መረጋጋት፤ እርካታ የለንም" የሚሉት ሐኪሟ፤ የጤና ባለሙያዎች ተረጋግተው እንዲሰሩ መንገዱ መመቻቸት አለበት ሲሉም ጠይቀዋል።

"መንግሥት ትንሽ ልክፈልሽ፤ በግል እንደፈለግሽ እያካካስሽ ነው ይላል። ስለተገደድኩ እንጂ እንደዚህ አልፈልግም" የሚሉት ዶ/ር ማህሌት፤ የጤና ባለሙያዎችም የግል ሕይወት እንዳላቸው በመጠቆም "አታግቡ አትውለዱ ልንባል አንችልም" ብለዋል።

በተለያዩ ጊዜያት ተመሳሳይ ጥያቄዎችን ያሰሙት ባለሙያዎቹ፤ የአሁኑ ጥያቄ ሲንከባለል የመጣ እና በኑሮ ውድነት እና ዋጋ ግሽበት ምክንያት የኅልውና ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል።

ከእንቅስቃሴው አስተባባሪዎች መካከል አንዱ የሆኑ ባለሙያ ከክፍያ ባለፈ "የጤና መድኅን የለንም። ብንታመም መታከም አንችልም። ስጋት ባለበት አካባቢ ነው እየሰራን ያለነው፤ እንደ አደጋ ተጋላጭነታችን አስፈላጊ የሆኑ ክፍያዎችን እያገኘን አይደለም። ለእነዚህ ጥያቄዎቻችን ምላሽ ይሰጠን የሚል እንቅስቃሴ ነው እያደረግን ያለነው" ብለዋል።

ጥያቄውን "ትክክለኛ እና ወሳኝ" የሚለው የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር፤ "የጤና ባለሙያው ተረጋግቶ ማኅበረሰቡን እንዲያገለግል ራሱ የተረጋጋ ሕይወት ሊኖረው ይገባል" ይላል።

የማኅበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መለሰ ባዕታ የጤና ባለሙያዎች የዓለም የጤና ድርጅት ባወጣው ደረጃ መከፈል እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ "[የጤና ባለሙያ] ስለሚበላው፣ ስለሚለብሰው እየተጨነቀ አንድን ማኅበረሰብ ስለ አመጋገብ ስርዓት ማስተማር እና ማከም በጣም የሚከብድ ነገር ነው" ብለዋል።

"አንቺ እየሞትሽ፤ ሌላውን እንዴት አድርገሽ ልታድኝው ትችያለሽ? በቅንነት እና በታማኝነት ማገልግል እንዳለ ሆኖ ለማገልገለም ቢያንስ መሠረታዊ [ፍላጎቶች] ሊሟሉለት ይገባል" ሲሉ አስረድተዋል።

ድምፃቸውን እያሰሙ ያሉ ባለሙያዎች እስራትን ጨምሮ ጫናዎች እየደረሱባቸው እንደሆነ ለቢቢሲ የተናገሩ ሲሆን፤ ማኅበሩ ይህን እርምጃ "ጥያቄ ለማዳፈን" የሚደረግ እና "አላስፈላጊ" ብሎታል።

'የመንግሥት አመራሮች ጥያቄዎቻችን ፖለቲካዊ ስም እየሰጧቸው ነው' የሚሉት የእንቅስቃሴው አስተባባሪ፤ "ፖለቲካዊ ፍላጎት የለንም፤ ፍላጎታችን በልተን ማደር ነው፤ ያስተማረንን ማኅበረሰብ አገልግለን መኖር ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

መንግሥት ለጥያቄዎቻቸው መልስ ካልሰጠ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ የተናገሩት የጤና ባለሞያዎች እና የእንቅስቃሴው አስተባባሪዎች፤ እስካሁን ከመንግሥት ተስፋ ሰጪ ምላሽ እንዳላገኙ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ለሥራ ማቆም አድማው በጣት የሚቆጠሩ ቀናት የቀሩ ሲሆን፤ በአድማው ወቅት ታካሚዎች እና ማኅበረሰቡ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳይደርስ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።

ቢቢሲ የጤና ሚኒስቴርን የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች ለማነጋገር ያደረገው ጥረት ባይሳካም የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ኃላፊ ዶ/ር ተገኔ ረጋሳ ለሪፖርተር በሰጡት ቃለ ምልልስ ጥያቄዎቹን "ተገቢ" ብለዋቸዋል።

ለጥያቄዎቹ ምላሽ ለመስጠት እየሰሩ መሆናቸውን የተናገሩት ኃላፊው፤ በቅርቡ የፀደቀው የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ በርካታ ችግሮችን እንደሚፈቱ ጠቁመዋል።

Monday, May 5, 2025

በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው ስለሚባለው 'አፈሳ' የነዋሪዎች ስጋት

 ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች ከመንገድ እየታፈሱመሆናቸውን ወላጆች፣ ወጣቶች እና ፖለቲከኞች በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየገለፁ ነው።



ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማ ነዋሪዎችም በግዳጅ የታፈሱ ወጣቶችን እንደሚያውቁ እና እነርሱም ባለባቸው ስጋት የተነሳ ድንገት ከተያዝን በሚል "ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ" ተናግረዋል።

ቢቢሲ ከአዲስ አበባ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው በአዳማ ከተማ የሚገኝ እና ከመንገድ ላይ ታፍሰው ታጉረውበታል የተባለን አንድ መጋዘን ተመልክቷል።

ይህ የማጎርያ መጋዘን በመንግሥት ባለቤትነት ስር ያለ ሲሆን በርካታ ወጣቶች በአዳራሹ አካባቢ ተሰብስበው ይታያል።

የመጋዘኑ መግቢያ አካባቢ ሰዎች እንዳይቀርቡ ገመድ የተወጠረ ሲሆን፣ የኦሮሚያ ሚሊሺያ የደንብ ልብስን የለበሱ የፀጥታ ኃይሎች ጥበቃ ያደርጉለታል።

ከመጋዘኑ ውጪ ልጆቻቸው እዚያ መጋዘን ውስጥ የሚገኙ ቤተሰቦች እንዲሁም ባሎቻቸው የተያዙባቸው ሴቶች ተሰብስበው ይታያሉ።

የተወሰኑት ሴቶች ጨቅላ ሕጻናትን ያዘሉ ሲሆን፣ ሌሎች ደግሞ ለቤተሰቦቻቸው የሚሰጥ ውሃ እና ምግብ ይዘዋል።

ቢቢሲ በዚህ የማቆያ መጋዘን አካባቢ ከተሰበሰቡ ሰዎች እንደተረዳው ወጣቶቹ ከመንገድ ላይ ከታፈሱ በኋላ በፀጥታ አካላት ወደዚህ ቦታ የመጡ ናቸው።

በኅዳር ወር የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደር አካላት እና የፀጥታ ኃይሎች ሕጻናት እና የአዕምሮ ህሙማንን ጨምሮ በርካቶችን የመከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀሉ በሚል በግዳጅ እንደያዙ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

በአዳማ ነዋሪ የሆነ እና ለደኅንነቱ በመስጋት ስሙን ከመናገር የተቆጠበ ወጣት ጓደኞቹ ከመንገድ ላይ ተይዘው መታሰራቸውን በመግለጽ እርሱም ስጋት እንደገባው ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ተናግሯል።

"ከምሽቱ 1 ሰዓት ከሆነ መንገድ ላይ አስቁመው ይወስዱሃል። ማንም ለምን እንደተያዝክ አይነግርህም። በመኪና ጭነው ይወስዱሃል" ሲል ያለውን ሁኔታ ገልጿል።

አክሎም "ገንዘብ ካለህ ግን ከተያዝክ በኋላም የመለቀቅ ተስፋ አለህ" ይላል።

"ባለፈው ምሽት እንዴት እንደተረፍኩ እኔ እና ፈጣሪ ነን የምናውቀው። መያዝ ብቻ ሳይሆን ገንዘብ ትጠየቃለህ። እንድትለቀቅ የምትፈልግ ከሆነ ገንዘብ እንድትከፍል ትጠየቃለህ" ሲል ይናገራል።

በቅርቡ ጓደኞቹ የደረሰባቸውንም በመግለጽ ሲያስረዳ "ሦስት ጓደኞቼን ሳር ተራ [አዳማ] አካባቢ በቁጥጥር ስር አዋሏቸው። በአስር ሺዎች የሚቆጠር ብር ጉቦ እንዲከፍሉ ተጠየቁ። ከዚያም እነርሱ ለመልቀቅ የግድ ሦስት ሰዎችን መተካት ነበረባቸው፤ የእነርሱን ቦታ ከተማ ውስጥ ዞር ዞር ብለው ሌሎች ሦስት ሰዎችን ይዘው ካመጡ በኋላ ነው እነዚህ ሦስቱን የለቀቁት" ይላል።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው በአዳማ የሚኖሩ ሌሎች ወጣቶች ድንገት በምሽት በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር ከዋልን በሚል ገንዘብ ይዘው አንደሚንቀሳቀሱ ተናግረዋል።

ይህ ስጋት የእነርሱ ብቻ ሳይሆን የቤተሰቦቻቸውም መሆኑን የተናገረው የአዳማ ነዋሪ "ወጣት ነኝ፤ ቤተሰብ መሥርቻለሁ። ልጅ አለኝ። ከተያዝኩ በሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ነኝ። ስለዚህ ሰዎች በብዛት ከሚታፈሱበት አካባቢ ርቄ ለመንቀሳቀስ እሞክራለሁ። ገፍቶ ከመጣ በሚል ደግሞ የምለቀቅበት ብር በኪሴ ይዤ እንቀሳቀሳለሁ" ይላል።

በአዳማ ከተማ የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር የሚያውሏቸው ሰዎች ቁጥር ለእያንዳንዱ ፀጥታ አባል እና ወረዳ አመራር ተተምኖ የተሰጠ መሆኑን እነዚህ ግለሰቦች ይናገራሉ።

ቢቢሲ በአዳማ ከተማ የሚካሄደውን አፈሳ እንዲሁም በአስተዳደሩ ላይ ስለሚቀርቡ ውንጀላዎች በተመለከተ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም።

ለቢቢሲ አስተያየታቸውን የሰጡ የአዳማ ከተማ ነዋሪ "አመራሮቹ ምን ያህል ሰዎች እንደሚጠበቅባቸው ተነግሯቸዋል፤ ስለዚህ ያገኙትን ያፍሳሉ። የተጣለባቸውን ኮታ ለመሙላት ሲሉ ጫማ በመጥረግ ሥራ ላይ የተሰማሩትን ሊስትሮዎች ሳይቀር በቁጥጥር ስር ያውላሉ" ብለዋል።

ሌላ የአዳማ ከተማ ነዋሪ በበኩሉ በተለያዩ አካባቢዎች ከመንገድ ላይ የሚታፈሱ ወጣቶች ላይ ድብደባ እና የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እንደሚፈጸም ይናገራል።

ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት እንዲሁም ከመከላከያ ሠራዊት እየታፈሱ በአዳራሽ ውስጥ ተይዘው ስለሚገኙ እና የመከላከያ ሠራዊት አባላት የግዳጅ ምልመላ ነው ስለሚባለው ጉዳይ ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም።

እስካሁን ድረስ የኦሮሚያ ክልል መንግሥትም ሆነ የፌደራል መንግሥት በግዳጅ እየታፈሱ ስለሚታሰሩ ሰዎች ያሉት ነገር የለም።

ከመከላከያ ሚኒስቴር የምልመላ መስፈርት ውጪ በግዳጅ የተያዙ ሕጻናትን እና ሰዎችን ለማስለቀቅ ቤተሰቦቻቸው ከፍተኛ ገንዘብ ጭምር እንዲከፍሉ ባለሥልጣናት ማስገደዳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኅዳር 26/2017 ዓ.ም. በምርመራ እንደደረሰበት መግለጹ ይታወሳል።

በወቅቱ አንዳንድ የኦሮሚያ ክልል የሚሊሻ አባላት ወጣቶችን ለመከላከያ ሠራዊት አባልነት ምልመላ በሚል ከያዙ በኋላ ለመልቀቅ ቤተሰቦቻቸው ገንዘብ እንዲከፍሉ ያስገደዱ መሆኑን ኮሚሽኑ አረጋግጫለሁ ብሏል።

በአንዳንድ አካቢዎች የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ከመስፈርት ውጪ የተደረገ ምልመላ መሆኑን በመግለጽ በክልሉ የፀጥታ አካላት የተያዙ ሰዎች ከማቆያ ስፍራዎች እንዲለቀቁ ያደረጉ መሆኑን መገንዘቡን ኢሰመኮ አመልክቷል።

ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ባሕሩ ጣሏቸው'፡ ትኩረት ያላገኘው የስደት መንገድ

 መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ 35 ዓመቱ ነው።

ከጂቡቲ ወደ የመን በጀልባ ያደረገውን የስደት ጉዞ አይረሳውም። በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለ ነበር የተሰደደው።



ሶማሊያን ጥሎ የወጣው የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ነበር።

ከአፍሪካ ወደ የመን የሚደረገው ስደተኞች የሚጓዙበት መንገድ 'ምሥራቃዊው ኮሪደር' በሚል ይታወቃል።

በብዛት ስደተኞች ከሚጓዙባቸው መንገዶች አንደኛው ነው። እምብዛም ግን ትኩረት አላገኘም።

ይህ መንገድ በጣም አደገኛው እንደሆነም መሐመድ ይናገራል።

"መንገድ ጀምረን 30 ደቂቃ ሳይሞላ ጀልባው ይዋዥቅ ጀመረ። የየመን ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች በአረብኛ ማውራት ጀመሩ። ስደተኞችን ከጀልባው ለመወርወር ነበር የሚመካከሩት። ከዚያም ሰባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አስገድደው ወደ ባሕሩ ጣሏቸው" ሲል ያስታውሳል።

መንገዱ አደገኛ ቢሆንም በየዓመቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች በዚህ መንገድ ይጓዛሉ።

ሚክስድ ማይግሬሽን ሴንተር እንደሚለው በየዓመቱ ከአፍሪካ ወደ የመን የሚገቡ ሰዎች 100 ሺህ ይደርሳሉ።

ስደተኞቹ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ናቸው። እንደ ሶማሊያ እና ጂቡቲ ካሉ የተቀሩት የምሥራቅ አፍሪካ አገራትም ዜጎች ይሰደዳሉ።

መሐመድ በተጓዘበት ጀልባ 47 ኢትዮጵያውያን፣ 5 ሶማሌያውየን እና 2 የየመን ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ነበሩ።

"በጣም አስጨናቂ ነበር። ውሃ ወደ ጀልባው ይገባል። ውሃውን ለማስወጣት ስንሞክር ነበር። በሕይወት መትረፋችንን እርግጠኛ አልነበርንም" ይላል።

ከአውሮፓውያኑ 2014 ጀምሮ የመን በእርስ በርስ ጦርነት እየተናጠች ነው። ስደተኞች ወደ ሳዑዲ አረቢያ መግባት ነው የሚፈልጉት። በሳዑዲ የሚፈለጉ ሠራተኞች ቁጥር ከፍተኛ ነው።

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም (አይኦኤም) እንደሚለው፣ አብዛኞቹ ስደተኞች ጥያቄያቸው የኢኮኖሚ ቢሆንም በተለይ ከአማራ ክልል እና ከኦሮሚያ ክልሎች የሚሰደዱት ወጣቶች ግጭት እና እስራትን በመሸሽ ነው

'ምሥራቃዊው መንገድ'

Skip podcast promotion and continue reading
የቢቢሲ አማርኛ ዋትስአፕ ቻናል
የቢቢሲ አማርኛ ዋትስአፕ ቻናል

ዜና፣ ትንታኔ እና ታሪኮችን በቀጥታ በዋትስአፕ ለማግኘት

ይህን በመጫን የቻናላችን አባል ይሁኑ!

End of podcast promotion

ሕገ ወጥ ስደተኞቹ ጂቡቲ በሚገኘው ኦቦክ በኩል አድርገው ደቡብ ምዕራብ የመን ወደሚገኘው ላሂጅ ይገባሉ።

ከሶማሊያ ቦሳሶ የሚነሱት ስደተኞች ደግሞ በየመን ደቡብ ምሥራቅ በሚገኘው ሻብዋህ የባሕር ዳርቻ ይደርሳሉ።

መሐመድ በሁለቱም መንገድ ተጉዟል። ከጂቡቲ ላሂጅ ለመድረስ አምስት ሰዓታት ወስዶበታል።

በአውሮፓውያኑ 2014 ወደ ሶማሊያ ከተመለሰ በኋላ በሶማሊያዋ ቦሳሶ በኩል ወደ የመን ገብቷል።

"በሁለተኛው ጉዞ አልፈራሁም። የመጀመሪያው ከጂቡቲ ያደረግኩት ጉዞ ረዥም ነበር። የመን ለመግባት 24 ሰዓት ወስዶብናል" ይላል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም እንደሚለው፣ ወደ የመን ለመሄድ ዋነኛው መንገድ ጂቡቲ ነው።

በአውሮፓውያኑ 2023 ብቻ 106 ሺህ ኢትዮጵያውያን ጂቡቲ ገብተዋል። ከአገራቸው ተነስተው የጂቡቲ ድንበር ለመድረስ ሳምንታት ይጓዛሉ።

ከአማራ ክልል የሚነሱ ስደተኞች ኦቦክ ለመድረስ 400 ኪሎሜትር ይጓዛሉ።

በመኪና፣ በአውቶብስ ወይም በእግር ነው ጉዞውን የሚያደርጉት። በጋ ላይ ሙቀቱ እስከ 50 ሴንቲግሬድ ይደርሳል።

ባሕር ዳርቻ ላይ ለሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች 300 ዶላር ከፍለው የኤደን ባሕረ ሰላጤን ለመሻገር ይሞክራሉ።

የሚክስድ ማይግሬሽን ሴንተር ቀጣናዊ ዳይሬክተር አይላ ቦንፊግሎ እንደሚሉት፣ ሕገ ወጥ የሰው ዝውውር ብዙዎች የተሰማሩበት ንግድ ነው።

"100 ሺህ ስደተኞች 300 ዶላር ቢከፍሉ 30 ሚሊዮን ዶላር የሚገኝበት ሥራ ነው ማለት ነው" ይላሉ።

በየመን የተዋቀረ መንግሥት አለመኖሩ ለሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም እንደሚለው፣ ባለፉት 10 ዓመታት ውስጥ 1,400 ስደተኞች በጉዞ ላይ ሳሉ ባሕር ውስጥ ሰጥመው ሞተዋል።

አይላ በበኩላቸው ቁጥሩ ከዚህም እንደሚበልጥ ይገምታሉ።

"ይህ ምሥራቃዊው የስደተኞች መንገድ በአህጉሪቱ በጣም አደገኛው ነው። በሕገ ወጥ መንገድ ባሕር ሲያቋርጡ የሚጠቀሙት የተበላሹ ጀልባዎች ነው" በማለት ለሚደርሰው አደጋ አንዱን ምክንያት ጥጠቅሳሉ።

ምን ያህል ስደተኞች እንደሞቱ በትክክል እንደማይታወቅ ያስረዳሉ።

ስደተኞች መንገድ ላይ ከሚገጥማቸው ፈተና ባሻገር በሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ብዝበዛም ይደርስባቸዋል።

"አምና 350 ስደተኞች አነጋግረን ነበር። ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ስለ ጉዞው የተዛባ መረጃ ሰጥተው እንዳሳሳቷቸው ይናገራሉ" ይላሉ አይላ።

"ሕገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎቹ ናቸው ለብዝበዛ የሚያጋልጧቸው። አካላዊ ጥቃት፣ ዝርፊያ እና ስቃይ ይደርስባቸዋል" ሲሉም ዳይሬክተሯ ያክላሉ።

አፍሪካውያን ስደተኞች ባሕሩን ከተሸገሩ በኋላም በሚደርሱባቸው አገራትም ለብዝበዛ ይጋለጣሉ።

በግጭት የምትናጠውን የመን ካለፉ በኋላ ሳዑዲ አረቢያ ቢገቡም ብዝበዛው ይቀጥላል።

"ጦርነቱ ጉዟችንን የበለጠ ከባድ አድርጎታል" ይላል መሐመድ።

ከየመን ሳዑዲ ለ11 ቀናት በእግር መጓዛቸውን ያስታውሳል። ያለ በቂ ምግብ እና ውሃ ነበር ድንበር የተሻገሩት።

"አንድ አብራን ትጓዝ የነበረች ሴት በረሃብ እና በውሃ ጥም ሞታለች" ይላል።

ሳዑዲም ስደተኞች ድንበሯን አቋርጠው እንዳይገቡ ትከላከላለች።

መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ
የምስሉ መግለጫ,መሐመድ አብዱላሂ ሞሐሙድ

በ2023 ሂውማን ራይትስ ዋች ባወጣው ሪፖርት የድንበር ጠባቂዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን መግደላቸውን ጠቁሟል።

ስደተኞቹ እና ጥገኝነት ጠያቂዎቹ ከየመን ወደ ሳዑዲ እየተሻገሩ ነበር።

በሳዑዲ የቤት ሠራተኛ ሆነው የተቀጠሩ እና በግንባታ ሥራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን ወደ 750 ሺህ እንደሚጠጉ ይገመታል።

የሚክስድ ማይግሬሽን ሴንተር ቀጣናዊ ዳይሬክተር አይላ እንደሚሉት፣ ስደተኛ ሠራተኞች መብታቸው ይገፈፋል።

"የሳዑዲ መንግሥት እንዳይዛቸው ተደብቀው ለመኖር ይገደዳሉ" ሲሉ ያስረዳሉ።

የሳዑዲ አረቢያ መንግሥትም ሕገ ወጥ ያላቸውን ስደተኞች ወደ አገራቸው ይመልሳል።

መሐመድ ሳዑዲ አምስት ዓመት ከሠራ በኋላ በ2021 በሳዑዲ መንግሥት ወደ ሶማሊያ ተመልሷል።

ሞቃዲሹ ውስጥ ሾፌር የሆነው መሐመድ የአምስት ልጆች አባት ነው።

ወደ ሶማሊያ መመለሱ ከባድ ቢሆንም ማንም ሰው እንዳይሰደድ ይመክራል።

"በአገራችሁ ተስፋ አትቁረጡ። ትዕግስት ይኑራችሁ። ያ የስደት መንገድ አሰቃቂ ነው" ይላል መሐመድ።

Monday, April 28, 2025

Ethiopia’s civil war: what’s behind the Amhara rebellion?

 Ethiopia is in the grip of a civil war between federal government forces and the Fano, a loose alliance of ethnic-based militia in the Amhara region.



This conflict in Ethiopia’s north erupted less than a year after the devastating Tigray war, which ended in 2022.

The Amhara are one of Ethiopia’s largest ethnic groups and played a leading role in the making of the Ethiopian state. Amharic serves as the country’s working language.

The region shares a border with Tigray. During the Tigray war, which began in 2020, various Fano groups allied with the federal government. A peace deal in 2022 to stop the war sidelined the Amhara militia groups, which strained relations with the government.

The Amhara conflict began as minor sporadic clashes with government forces in April 2023. This rapidly escalated into a full-scale insurgency by August when Fano forces launched a full blown attack in an effort to control the region’s major cities.

The violence since has displaced more than 100,000 people and left 4.7 million children out of school.

The death toll from the conflict is piling up. In March 2025, the government claimed to have killed more than 300 Fano fighters.

We are researchers studying ethnic nationalism, social movements and insurgency in Ethiopia, with a focus on Amhara. Based on our studies into the Fano and ongoing research on Ethiopia’s political reforms process, we see three factors behind the escalating armed struggle in Amhara:

  • a mismanaged political transition from 2018 to 2020

  • fallout from the 2020-2022 Tigray war

  • a hollow pursuit of peace.

Mismanaged transition

Between 1991 and 2018, Ethiopia was governed by the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front. This was a powerful coalition of four ethno-national parties representing Tigray, Amhara, Oromo, and Southern nations, nationalities and peoples.

Faced with a political crisis and growing unrest in 2014 following opposition clampdowns and arbitrary arrests, the coalition needed a change. Two members – the Oromo People’s Democratic Organisation and the Amhara National Democratic Movement – joined forces to oust the Tigray People’s Liberation Front from its dominant position. They did this by leveraging youth-led protests, which played out between 2015 and 2018.

Following the resignation of prime minister Hailemariam Desalegn in 2018, the two parties orchestrated Abiy Ahmed’s ascent to power.

For a moment, the relationship between the Oromo and Amhara wings of the coalition looked like one of equals. This didn’t last. In December 2019, Abiy merged the coalition into a single party, the Prosperity Party.

The Oromo wing positioned itself as the core of the Prosperity Party. It monopolised key political positions and economic opportunities. This included asserting control over the capital, Addis Ababa.


Read more: Abiy Ahmed gained power in Ethiopia with the help of young people – four years later he's silencing them


Amhara’s outspoken leaders who criticised this dominance faced removal, arrest or exile. The region’s president, Ambachew Mekonnen, was assassinated in June 2019.

Harassmentkidnappings for ransom and arrests were daily experiences for Amhara region residents trying to enter Addis Ababa. Members of the Amhara community also faced ethnic-based violence in various parts of the country.

These incidents provoked anti-government protests throughout Amhara.

Fallout from the Tigray war

peace agreement signed in 2022 in South Africa ended a brutal two-year war in Tigray and neighbouring regions. However, it deepened the sense of marginalisation in Amhara.

While the agreement silenced the guns in Tigray, it sidelined Amhara constituencies by denying them representation in the talks despite the region being affected by the war. The agreement’s ambiguity regarding the fate of territories disputed between Amhara and Tigray, such as Welkait, further fuelled distrust.

The last nail in the coffin came in April 2023. The government decided to dismantle regional special forces. This was ostensibly aimed at consolidating the country’s fighting forces.

However, with unresolved territorial disputes and Oromo nationalist ambitions at the centre, disarming the Amhara Special Forces was interpreted as a move to weaken Amhara defences. Additionally, the more than 200,000-strong Tigray Defence Forces were left intact. This contributed to a sense of vulnerability in neighbouring Amhara.

Public protests led to clashes with government forces. These protests morphed into an insurgency by the Fano in the following months.

The insurgency has expanded its reach and has public support across the region and in the diaspora.

The Fano insurgency is taking place in a territory three times the size of Tigray, stretching the federal army.

Various Fano factions cite objectives that range from the protection of Amhara interests to constitutional change and overthrowing the federal government.

However, the insurgency is still in its infancy. It lacks unified leadership, a cohesive structure or a chain of command. Factional divisions and competition persist, and there are no clear objectives.

Hollow pursuit of peace

The government seems determined to crush the Fano insurgency by force. A state of emergency was declared in August 2023 for six months. It was later extended.

While the state of emergency in Amhara officially ended in June 2024, some restrictions remain in place. This includes de facto curfews in major cities, including the capital Bahir Dar.

The counterinsurgency relies on heavy Ethiopian National Defence Forces deployments and drone strikes.

On the other hand, the government has indicated its openness to peace talks. However, it has avoided meaningful confidence-building measures, such as releasing Amhara political prisoners. A Peace Council established to mediate between the Fano and the government has proven ineffective. Its spokesperson has noted federal reluctance to negotiate.


Read more: Ethiopia's war may have ended, but the Tigray crisis hasn't


The government’s peace efforts have centred on repeated calls for insurgents to surrender. There are reports that the government wants to talk to different Fano factions separately in the hope of fragmenting the insurgency further. Secret talks with one faction of the Fano are an indication of this strategy.

The path forward

The government’s violent counterinsurgency and occasional peace overtures are unlikely to succeed. The Prosperity Party is not popular in Amhara. A meaningful peace process – rather than calls for surrender or attempts to co-opt factions – is essential. This should start with measures like releasing arbitrarily detained Amhara activists, journalists, academics and politicians.

The federal government also needs to be part of a multi-stakeholder negotiation involving all Fano factions, civil society, community leaders, and domestic and diaspora-based opposition groups. Unbiased mediation from regional and international players may also be useful. Past attempts at piecemeal talks with factions of armed groups – be it in Tigray or Oromia – have prolonged insurgencies or fostered new ones. Only a comprehensive, all-inclusive dialogue can address the crisis.

Such a process needs to address deep-seated structural challenges. This includes ensuring the protection of Amhara minorities living in other regions, and the region’s representation within local, regional and federal government structures. Territorial disputes need to be addressed through a process rooted in historical context, constitutional principles and the consent of the people concerned.

Ultimately, enduring peace requires ending the cycle of ethnic dominance in Ethiopia’s federal governance arrangement.

Source: https://theconversation.com/ethiopias-civil-war-whats-behind-the-amhara-rebellion-252425

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time