Wednesday, August 30, 2017

ለካርታውስ ይቅርታ ተጠየቀ! ሕገ መንግሥቱ እንዴት ይስተባበል?

Image may contain: text
ለካርታውስ ይቅርታ ተጠየቀ! ሕገ መንግሥቱ እንዴት ይስተባበል?

ሰሞኑን በኢቢሲ የተላለፈውን ካርታ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ብዙ አነጋግሯል፤ ከዚያም አልፎ ‹‹ይቅርታ›› ተጠይቆበታል- ማዘናጊያ ቢሆንም፡፡ 
ግን የአማራ ‹‹ክልል›› ከሱዳን ጋር እንደማይዋሰን የሚያሳየው ካርታ በሕግ የጸና መሆኑን ስንቶቻችን እናውቃለን? ቤኒሻንጉል ጉምዝና የትግራይ ክልሎች ጎረቤት መሆናቸውን በሕግ የተደነገገ መሆኑን ስንቶቻችን ተገንዝበናል? 

ከሽግግሩ መንግሥት በኋላ የተቋቋሙ ‹‹ክልሎች›› የራሳቸውን ሕገ መንግሥት አጽድቀዋል፡፡ ከነዚህም አንዱ የጎጃም ለም መሬቶችን ይዞ የተቋቋመው ‹‹ክልል›› ቤኒሻንጉል ጉምዝ ነው፡፡ በዚህ ክልል ሕገ መንግሥት መሠረት የአማራ ‹‹ክልል›› ከሱዳን ጋር አይጎራበትም፡፡ በ1988 ዓም በጸደቀው በክልሉ ሕገ መንግሥት መሠረት ክልሉን በሰሜን በኩል የሚያዋስነው የትግራይ ክልል እንደሆነ ቁጭ አድርጎ በአንቀጽ ሁለት ይናገራል፡፡ በዚህ መሠረት እነ ጃዊ፣ ቋራና መተማ የቤኒሻንጉል ሲሆኑ እነ አርማጭሆ ደግሞ ከወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ጋር የትግሬ ሆነዋል ማለት ነው፡፡ ትግርኛ ስለማልችል የታላቋ አዲ ትግራይ ሕገ መንግሥት ምን እንደሚል አላውቅም፡፡ 

አሁን ጥያቄው የካርታውስ ጉዳይ በይስሙላ ይቅርታ ታለፈ! የተሰረቀው ተራራና የተሰረቀው ቤተ መቅደስም አፉ በሉን ተብሎ ተመለሠ፡፡ ይህ ሕገ መንግሥት ምን ዓይነት ማስተካከያ ሊደረግበት ነው? የሚለው ነው፡፡ 
ይህን የያዘውን የቤኒሻንጉል ክልል ሕገ መንግሥት ክፍል በፎቶው ላይ ይመልከቱ፡፡ Read more here
No automatic alt text available.

No comments:

Post a Comment

Related Posts Plugin for WordPress, Blogger...

Recent Articles

Recent Video Uploads

Subscribe Ethiopia Today Videos and Watch on You Tube

Ethiopia Today

  • Active a minute ago with many
  •  
  •  videos
Ethiopia Today bringing you recent information about Ethiopia. It bring you, news, Amharic movies,  Musics and many clips. subscribe and get many Videos on time